🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ ግብጽ በዓባይ ወንዝ ላይ የምታራምደው የቅኝ ግዛት ትርክት አክትሟል ሲሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ገለጹ።
በቅኝ ግዛት ዘመን አስተሳሰብ ጥቅምን ማረጋገጥ እንደማይቻልም ነው ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) የተናገሩት።
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቆይታ የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሐመድ አብደላቲ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ የሰጡትን አስተያየት በጽኑ አውግዘዋል።
ግብጽ ሰላም እና መረጋጋትን አደጋ ላይ ከሚጥሉ አፍራሽ ንግግሮች እና ድርጊቶች መቆጠብ እንደሚገባት ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ግብጽ በዓባይ ወንዝ ላይ የምታራምደው የቅኝ ግዛት ትርክት አክትሟል ሲሉም ነው የገለጹት።
የግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የኢትዮጵያ አቋም የተናጠል እርምጃ ነው ማለታቸው የዘመኑን እውነታ የማይመጥን የቅኝ ግዛት እሳቤ መሆኑን አመልክተዋል።
ሚኒስትሩ ግብጽ በናይል ወንዝ እኔ ብቻ የበላይነቱን ልውሰድ የሚል ጊዜ ያላፈበት ትርክት ተቀባይነት እንደሌለው ገልጸው መሰል እሳቤዎች ከሀገር ባለፈ ቀጣናዊ መረጋጋትን ስጋት ውስጥ የሚከቱ ናቸው ብለዋል።
አስተያየቱ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የሚቃረን ተቀባይነት የሌለው ሀሳብ መሆኑንም አመልክተዋል።
ግብጽ ኢትዮጵያ እንዳትረጋጋ ተላላኪ ቡድኖችን በመመልመል እና በማሰማራት እየደገፈች መሆኑን ገልጸው ይህን አካሄድ ኃላፊነት የጎደለውና ጠብ አጫሪ ድርጊት ሲሉም ገልጸውታል።
ከውሃ መብቶች እና ቀጣናዊ ትብብር አንጻር ሀሳባቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ የናይል ወንዝ አብዛኛው ድርሻ የምትወስደው ኢትዮጵያ ሀብቷን የመጠቀም ህጋዊ መብት እንዳላትም ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ሕጋዊና በመርህ ላይ የተመሰረተ መሆኑን ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) አመልክተዋል።
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይህን የኢትዮጵያ መብት እውቅና እየሰጠው እንደሚገኝም ነው የተናገሩት።
ግብጽ በናይል ውሃ ላይ ብቻዬን ልጠቀም በሚል እያራመደች ያለችው አቋም ጊዜ ያለፈበትና የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ መሆኑን ጠቁመው ወቅቱ ከሚጠይቀው አስተሳሰብ እና አካሄድ ጋር የማይሄድ ነው ብለዋል።
ግብጽ በዓባይ ወንዝ ላይ የምታራምደው የቅኝ ግዛት ትርክት አክትሟል ሲሉም ነው ያስገነዘቡት።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026