🔇Unmute
ሠመራ፤ ታህሳስ 28/2018(ኢዜአ)፦ በሰመራ ሎጊያ ከተማ የበዓል ገበያ የእርድ እንስሳት አቅርቦቱ የተሻለ በመሆኑ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመቱ እንደሚገኙ ሸማቾች ተናገሩ።
ለገና በዓል የእርድ እንስሳት አቅርቦትን በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሰመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የተሻለ አቅርቦት በመኖሩ በዓሉን ማክበር የሚያስችለንን የእርድ እንስሳት መግዛት ችለናል ብለዋል።

በከተማዋ በሚገኘው ገበያ ለእርድ የሚሆኑ ፍየሎችና በጎች በብዛት በማግኘታቸው አማርጠው መግዛት መቻላቸውን የተናገሩት አቶ ወንደሰን እምሩ ናቸው።
በዓሉን ማክበር የሚያስችሉ በተለይ ለእርድ የሚሆኑ ፍየሎችን በተሻለ አማራጭ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
በዚሁ ዕለት ለበዓል የሚሆን የእርድ እንስሳ የሸመቱት ሳሙኤል አየለ ከባለፈው ዓመት ብዙም ባልተራራቀ ዋጋ የሚፈልጉትን መግዛታቸውን ገልጸዋል።

በተለይ የፍየል ገበያው የተሻለ አቅርቦት ስላለው አማርጠው መግዛታቸውን ነው የተናገሩት።
ሌላኛዋ ሸማች ወይዘሮ ብዙአየሁ አወቀ በገበያው የፈለጉትን መሸመታቸውን ገልጸው፤ አቅርቦቱ የተሻለ መሆኑን ቁመዋል።
የሚያረቡትን ፍየሎች ለገበያ ይዘው የቀረቡት አሩሱ ዑመር በበኩላቸው ገበያው ከባለፈው ዓመት ጋር በዋጋ ረገድ ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
ይዘው ገበያ የወጡትን ፍየሎች በተሻለ ዋጋ እየሸጡ መሆናቸውን ገልፀዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025