የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በሰመራ ሎጊያ ከተማ የበዓል ገበያ የእርድ እንስሳት አቅርቦቱ የተሻለ በመሆኑ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመትን ነው

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሠመራ፤ ታህሳስ 28/2018(ኢዜአ)፦ በሰመራ ሎጊያ ከተማ የበዓል ገበያ የእርድ እንስሳት አቅርቦቱ የተሻለ በመሆኑ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመቱ እንደሚገኙ ሸማቾች ተናገሩ።

ለገና በዓል የእርድ እንስሳት አቅርቦትን በተመለከተ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሰመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የተሻለ አቅርቦት በመኖሩ በዓሉን ማክበር የሚያስችለንን የእርድ እንስሳት መግዛት ችለናል ብለዋል።


በከተማዋ በሚገኘው ገበያ ለእርድ የሚሆኑ ፍየሎችና በጎች በብዛት በማግኘታቸው አማርጠው መግዛት መቻላቸውን የተናገሩት አቶ ወንደሰን እምሩ ናቸው።

በዓሉን ማክበር የሚያስችሉ በተለይ ለእርድ የሚሆኑ ፍየሎችን በተሻለ አማራጭ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

በዚሁ ዕለት ለበዓል የሚሆን የእርድ እንስሳ የሸመቱት ሳሙኤል አየለ ከባለፈው ዓመት ብዙም ባልተራራቀ ዋጋ የሚፈልጉትን መግዛታቸውን ገልጸዋል።


በተለይ የፍየል ገበያው የተሻለ አቅርቦት ስላለው አማርጠው መግዛታቸውን ነው የተናገሩት።

ሌላኛዋ ሸማች ወይዘሮ ብዙአየሁ አወቀ በገበያው የፈለጉትን መሸመታቸውን ገልጸው፤ አቅርቦቱ የተሻለ መሆኑን ቁመዋል።

የሚያረቡትን ፍየሎች ለገበያ ይዘው የቀረቡት አሩሱ ዑመር በበኩላቸው ገበያው ከባለፈው ዓመት ጋር በዋጋ ረገድ ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ተናግረዋል።

ይዘው ገበያ የወጡትን ፍየሎች በተሻለ ዋጋ እየሸጡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.