የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘላቂ የገቢ እድገትን የማረጋገጥ ስራዎች ተከናውነዋል-ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በገቢዎች ዘርፍ ተቋማዊ የማስፈጸም አቅም የማሳደግ፣ዘመናዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓት የመገንባት፣ የታክስ ህግ ተገዢነትት የማረጋገጥ እና ዘላቂ የገቢ እድገትን የማረጋገጥ ስራዎች ተከናውነዋል ሲሉ ‎የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ ተናገሩ።

‎‎ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተገናኘ ዘመናዊ የግብር ስርዓትን ለመዘርጋት መሰራቱን ያስታወሱት ሚኒስትሯ በ2011 በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ታክስ በማሳወቅ ረገድ 10.1 % በመቶ ብቻ የነበረው አሰራር በ2017 ዓ.ም 94 በመቶ የሚሆኑ ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በኢ-ፋይል ማሳወቃቸውን ተናግረዋል።

በተመሳሳይ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ግብር የከፈሉ የግብር ከፋዮች በ2011 ከነበረበት ዝቅተኛ ደረጃ በ2017 ወደ 64 በመቶ ማሳደግ ተችሏል ነው ያሉት።

ዘመናዊ የግብር ስርዓትን በማጠናከር ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እና የታክስ ተደራሽነትን ለማስፋት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጠሉም ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።

‎‎በ2018 ባለፉት ስድስት ወራት 709 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል ብለዋል። ይህ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ256 ቢሊየን ብር ብልጫ ያለው መሆኑን ጠቁመዋል።

በ2018 በጠቅላላው 2 ነጥብ 1 ትሪሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

በቀጣይም ቴክኖሎጂ መር የታክስ አስተዳደርን የበለጠ በመዘርጋት የታክስ ስወራን መከላከል፣ በግብር ከፋዩ እና በታክስ አስተዳደሩ መካከል መተማመን ላይ የተመሰረተ የታክስ ስርዓትን ለመከተል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.