🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ ዘርፉ ኢኖቬሽን እና ስራ ፈጠራን በመደገፍ ለሃገራዊ እድገቱ የበኩሉን እንዲወጣ ለማድረግ የተጀመሩ የለውጥ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉየኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርሃና ተኹልቁ ገለጹ፡፡
ሃገራዊ ለውጡ ለኢኮኖሚው ስርዓት ካስተዋወቃቸው ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን አንዱ ነው።
ይህ ባለስልጣን የካፒታል ገበያ ስርዓትን ፈጠራን በማበረታታት በካፒታል ፈላጊዎች እና ካፒታል አቅራቢዎች መካከል ድልድይ የሚሆን ስርዓት እየገነባ መሆኑ ተመላክቷል።
በኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቀው የካፒታል ገበያ ስርዓት ባለፉት ዓመታት የተለያዩ ሂደቶችን አልፎ ሶስት ቁልፍ ተቋማትን መፍጠር መቻሉን የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርሃና ተኹልቁ ተናግረዋል።
እነዚህም የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ገበያ እና የማዕከላዊ ሰነደ ሙዓለንዋዮች ግምጃ ቤት መሆናቸውን ጠቁመዋል።
እነዚህ ተቋማት ከማቋቋም ባለፈ የካፒታል ገበያ አገልግሎት የሚሰጡ 15 ተቋማት ፈቃድ አግኝተው ወደ ስራ መግባታቸውንም አስታውቀዋል።
ተቋማቱም የተከፈለ ካፒታላቸው 1.5 ቢሊየን ብር መድረሱን እና በተጨማሪም 10 ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለንዋይ ገበያ ላይ ለመመዝገብ ሂደት ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በባንኮች መካከል በገበያ ላይ የተመሰረተ የገንዘብ ልውውጥ እያደገ መጥቷልም ብለዋል። በቀጣይ ዘርፉ ኢኖቬሽን እና ስራ ፈጠራን በመደገፍ ለሃገራዊ እድገቱ የበኩሉን እንዲወጣ ለማድረግ የተጀመሩ የለውጥ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ መናገራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025