የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለፋይናንስ ተቋማት የደንበኞች አገልግሎትን ለማፋጠንና ደህንነቱን ለማስጠበቅ ትልቅ እገዛ ያደርጋል

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጭሮ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፡- ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የፋይናንስ ተቋማት ደንበኞችን መረጃ አያያዝ ለማዘመን፣ ፈጣንና ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ተገለጸ።

ኢዜአ በጭሮ ከተማ ከሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች ጋር በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት ላይ ቆይታ አድርጓል።

የስራ ሀላፊዎቹ እንዳሉት ዲጂታል መታወቂያው የደንበኞች የዓይን፣ የፊት ገፅታና አሻራ በኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ በመያዝ አንድ ሰው ወጥ መረጃን ለመያዝ ከማጭበርበር የፀዳ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የጭሮ ኦዳ ቡልቱም ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ በላይ የሗላሸት እንዳሉት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በሐሰተኛ መታወቂያ የሚፈጸሙ የማጭበርበር ተግባራትን ለመከላከል ያስችላል።

የዲጂታል መታወቂያ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ መረጃ መያዙ ተገልጋዩ አንድ ማንነት እንዲኖረው በማድረጉ ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባንኩ አዲስ ለጀመረው የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጠን የማሻሻል ስራን የሚያቀላጥፍ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በአዋሽ ባንክ የጭሮ ቅርንጫፍ የደንበኞች አገልግሎት እና ኦፕሬሽን ስራ አስከያጅ አቶ ቴዎድሮስ ሰለሞን በበኩላቸው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ደንበኞችንና ባንኮች በተሟላ መልኩ እንዲተዋወቁ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያቀላጥፍ ነው።

ደንበኛው በአንድ የፋይዳ ቁጥር ብቻ በመመዝገቡ ባንኮች የብድር አገልግሎት ሲሰጡ ደንበኞቻቸውን በሚገባ እንዲያውቁና የብድር ክትትሉን በተገቢው መልኩ እንዲያከናውኑ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በፋይናንስ ተቋማት ውስጥ እየተተገበረ ያለውን ከወረቀት ነፃ አገልግሎት ለማቀላጠፍ የሚያግዝ ነውም ብለዋል።

በኢትዮ ቴሌኮም የጭሮ ማዕከል ሽያጭ ባለሙያ አቶ ተንኮሉ በቀለ በበኩላቸው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የአንድ ሰው መረጃን ወጥነት ባለው መንገድ በመመዝገብ ፈጣንና ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ የሚያሰፍን መሆኑን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026