🔇Unmute
ጭሮ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፡- ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የፋይናንስ ተቋማት ደንበኞችን መረጃ አያያዝ ለማዘመን፣ ፈጣንና ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ተገለጸ።
ኢዜአ በጭሮ ከተማ ከሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች ጋር በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት ላይ ቆይታ አድርጓል።
የስራ ሀላፊዎቹ እንዳሉት ዲጂታል መታወቂያው የደንበኞች የዓይን፣ የፊት ገፅታና አሻራ በኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ በመያዝ አንድ ሰው ወጥ መረጃን ለመያዝ ከማጭበርበር የፀዳ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የጭሮ ኦዳ ቡልቱም ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ በላይ የሗላሸት እንዳሉት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በሐሰተኛ መታወቂያ የሚፈጸሙ የማጭበርበር ተግባራትን ለመከላከል ያስችላል።
የዲጂታል መታወቂያ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ መረጃ መያዙ ተገልጋዩ አንድ ማንነት እንዲኖረው በማድረጉ ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባንኩ አዲስ ለጀመረው የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጠን የማሻሻል ስራን የሚያቀላጥፍ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በአዋሽ ባንክ የጭሮ ቅርንጫፍ የደንበኞች አገልግሎት እና ኦፕሬሽን ስራ አስከያጅ አቶ ቴዎድሮስ ሰለሞን በበኩላቸው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ደንበኞችንና ባንኮች በተሟላ መልኩ እንዲተዋወቁ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያቀላጥፍ ነው።
ደንበኛው በአንድ የፋይዳ ቁጥር ብቻ በመመዝገቡ ባንኮች የብድር አገልግሎት ሲሰጡ ደንበኞቻቸውን በሚገባ እንዲያውቁና የብድር ክትትሉን በተገቢው መልኩ እንዲያከናውኑ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በፋይናንስ ተቋማት ውስጥ እየተተገበረ ያለውን ከወረቀት ነፃ አገልግሎት ለማቀላጠፍ የሚያግዝ ነውም ብለዋል።
በኢትዮ ቴሌኮም የጭሮ ማዕከል ሽያጭ ባለሙያ አቶ ተንኮሉ በቀለ በበኩላቸው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የአንድ ሰው መረጃን ወጥነት ባለው መንገድ በመመዝገብ ፈጣንና ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ የሚያሰፍን መሆኑን ጠቁመዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026