የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የወጣቶችን የፈጠራ አድማስ የሚያጎለብቱ የሥልጠና ዘርፎች እየተሰጡ ነው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦የወጣቶችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትና የፈጠራ አድማስ የሚያጎለብቱ ዘመኑን የዋጁ አዳዲስ የክህሎት ማበልጸጊያ የሥልጠና ፕሮግራሞች እየተተገበሩ መሆኑን የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ወጣቶች ችሎታቸውንና ሀሳባቸውን ትርጉም ወዳላቸው ፈጠራዎች መቀየር የሚያስችል "ክህሎት ኢትዮጵያ" የተሰኘ መርሃ ግብር ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ሦስተኛውን ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ባስጀመረቡት ወቅት፤ የክህሎት ኢትዮጵያ እሳቤ ወጣቶች የማህበረሰቡን አንገብጋቢ ፍላጎቶች እንዲመረምሩና ሀገራቸውን የሚጠቅሙ መፍትሔዎችን እንዲፈጥሩ የሚያስችል ነው ማለታቸው ይታወሳል።

የወጣት ፈጣሪዎችን የማምረት አቅም ለማሳደግ ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባም አፅንኦት ሰጥተዋል፡፡

የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የመጪው ዘመን የመወዳደሪያ መድረክ ነው፡፡

የዓለም ሁኔታ ሙያና ክህሎትን የሚያበረታታ ቢሆንም በኢትዮጵያ ለክህሎት ያለን ግንዛቤ ገና አላደገም ነው ያሉት።

ክህሎት የዘመናዊው ዓለም የመወዳደሪያ መስክና ጸጋ መሆኑን ገልጸው፤ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና እንደ ሁለተኛ ምርጫ መታየት የለበትም ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከለውጡ ወዲህ ያላትን የወጣቶቿን እምቅ አቅም ታሳቢ ያደረገ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በዓለም ላይ መሪ የሆኑ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የክህሎት ትሩፋቶች መሆናቸውን በማንሳት፤ በኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሥልጠናና የቅበላ አቅም እያደገ መምጣቱን አንስተዋል፡፡

የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የዘመኑ ኢንዱስትሪ የሚፈልጋቸውን ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ለማፍራት ነባር የሥልጠና ዘርፎችን እያሻሻለና አዳዲሶችን ገቢራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በዚህም በ2018 ዓ.ም የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት፣ ባዮ ሜዲካል ቴክኖሎጂ፣ ፕላስቲክ ቴክኖሎጂ፣ ሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ እና ማንፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂን ጨምሮ 11 አዳዲስ የሥልጠና መስኮች ተጀምረዋል ብለዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ወደ ሥልጠና የሚገቡ ወጣቶችን ቁጥር ከማሳደጉም በላይ፤ አዳዲስ የሥልጠና ዘርፎችን ዘመኑን በዋጁ ቴክኖሎጂዎች አስደግፎ እየሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ይህም ከንድፈ ሀሳብ የትምህርት አሰጣጥ ይበልጥ ለተግባር ሥልጠና ያተኮረ እንዲሆን አስችሎታል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ በመደበኛና አጫጭር ሥልጠናዎች ስድስት ሚሊዮን ዜጎችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ሰልጣኞች ከሀገር ውስጥ ባሻገር ድንበር ተሻጋሪ አቅም እንደሚገነቡም ተናግረዋል፡፡

ለዚህ ደግሞ መንግስት የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የስልጠና ዘርፎች ሙያን በተግባር ማስተማር በሚችሉ ዘመኑ ባፈራቸው ግብዓቶች እንዲሟሉ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም ወጣቶች መሰልጠን፥ ለሥራ መዘጋጀትና ችግርን የመፍታት አቅምን ማዳበር መሆኑን ተረድተው ወደ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026