የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ የተቀናጀ የግብርና አሰራር ስርዓትን በመተግበር የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ):- በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተቀናጀ የግብርና አሰራር ስርዓትን በመተግበር የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉ ተመላከተ።

በክልሉ ጉራጌ ዞን በምግብ እና በሃድያ ዞን በእንስሳት ሀብት ልማት ማጠናከሪያ ፕሮግራም እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ላይ የመስክ ምልከታ ተካሄዷል፡፡


የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የተሰሩ የመስኖ ልማት፣ በክላስተር የለማ የቡና ማሳና የቡና ችግኝ ጣቢያ ላይ ምልከታ የተደረገ ሲሆን በጎታም ወንዝ ላይ የተገነባው ድልድይም ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ አህመድ ሀቢብ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ እየተተገበሩ ያሉ የግብርና ኢኒሼቲቮች የአርሶ አደሩን ህይወት እየቀየሩ መሆኑን ተናግረዋል።


በግብርናው ዘርፍ አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ ለወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር፣ ለኢንዱስትሪ በቂ ምርት ለማቅረብና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለመተካት የሚያስችል ዕድል እየተፈጠረ ነው ብለዋል።

ከዚህም ባለፈ ዝርያቸው የተሻሻሉ እና ምርታማ የሆኑ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ ተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን ማጎልበት እየተቻለ መሆኑን ጠቁመዋል።

በግብርና ሚኒስቴር የስርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም ብሔራዊ አስተባባሪ አቶ ከበሩ በላይ በበኩላቸው በምርምር፣ በውሃ እና መስኖ፣ በቴክኖሎጂ፣ በግብዓት አቅርቦት፣ በገበያ መሰረተ ልማት ግንባታና ትስስር ስኬታማ ስራዎች ተመዝግበዋል ብለዋል።


የአርሶ አደሩ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ በምግብ ራሱን እንዲችል ከማድረግ ባለፈ ያመረተውን ምርት ወደ ገበያ በማውጣት ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ የማድረግ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።

የስርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራሙ በክልሉ በአራት ዞኖች በሚገኙ አስር ወረዳዎች ከ78 በላይ በሚሆኑ ፕሮጀክቶች በስኬት እየተከናወነ መሆኑንም አንስተዋል።

በክልሉ የቸሀ ወረዳ ነዋሪው አቶ ጀማል ባድሳዊ መንግስት ጥምር ግብርና ላይ እንዲያተኩሩ በማድረግ ምርትና ምርታማነታቸውን በማሳደግ ህይወታቸው መቀየሩን ተናግረዋል ።

ክፍት የተደረገው የጎታም ድልድይ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው ያመረቱትን ምርት ወደ ገበያ ለማውጣት እና የግብርና ግብዓትን በወቅቱ ለማግኘት እንደሚያስችላቸውም ተናግረዋል።

በቀረበላቸው የሶላር ቴክኖሎጂ ተጠቅመው ከወንዝ ውሃ በመጥለፍ በማህበር ተደራጅተው አትክልትና ፍራፍሬ በማምረት ለገበያ እያቀረቡ መሆናቸውን የተናገረችው ደግሞ ወይዘሪት አምሪያ ሙንታቃ ናት።


በመስክ ምልከታው መርሐ ግብር ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞን እና የወረዳ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የህብረተሰብ ክፍሎች እና የአለም ባንክ የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026