የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በከተማዋ በተያዘው በጀት ዓመት ለአንድ መቶ ሺህ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ ለማዳረስ እየተሰራ ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደገሃቡር፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦በሶማሌ ክልል ደገሃቡር ከተማ በተያዘው በጀት ዓመት ለአንድ መቶ ሺህ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አብዲሀኪም መአሊን ገለጹ።

የደገሃቡር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዲሀኪም መአሊን ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዜጎች ወጥ የሆነ ማንነት እንዲኖራቸው በማድረግ የተቀላጠፈና ዘመናዊ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው።

ፋይዳ መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ ነው

ፋይዳ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተቀመጠው ሀገራዊ ግብ እንዲሳካና ለዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ብለዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት በከተማዋ 100 ሺህ ዜጎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እስካሁን ከ30 ሺህ በላይ ለሚሆኑት ተደራሽ መደረጉን አመልክተዋል።

በከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል።

ስልጠናው በቴክኖሎጂ የዳበረ ወጣት ለመፍጠር የላቀ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፣ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ዜጎች የዲጂታል መታወቂያውን በመያዝ ከሚሰጡ ዘመናዊ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026