የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በዓድዋ ድል የታየውን አርበኝነት፣ የባቡር መሰረተ ልማትን በራስ አቅም በውጤታማነት በመገንባት እንደግመዋለን

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦ በዓድዋ ድል የታየውን አርበኝነት፣ የባቡር መሰረተ ልማት ስራዎችን በራስ አቅም በፍጥነትና በውጤታማነት በማጠናቀቅ ደግመን እናሳያለን ሲሉ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለጹ።

ከዐድዋ ተራሮች እስከ ጉባ፤ ዐድዋ በልኩ ሲዘከር!

‎የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር 130ኛውን የዓድዋ ድል በዓል አክብሯል።

በዓሉን በማስመልከት በራስ አቅም እየተገነባና እየተጠናቀቀ የሚገኘው የኤ.ኤም.ጂ ኢንዱስትሪ ፓርክን ከኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር የሚያገናኘው የሶስት ኪሎ ሜትር የባቡር መሰረተ ልማት ተጎብኝቷል።


በጉብኝቱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ፣ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ኢንጂነር ታከለ ኡማ ፤ አባቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነት ታላቁን የዓድዋ ድል ታሪክ አስረክበውናል ብለዋል።


‎እኛ ደግሞ ለቀጣዩ ትውልድ ስንቅ የሚሆን አኩሪ የባቡር ትራንስፖርት መሠረት ልማት በራስ አቅም እየገነባን እንገኛለን ብለዋል።

እየተገነቡ የሚገኙት የባቡር መሰረተ ልማቶች ነገ ላይ ከዚህ የተሻለና የበለጠ ሥራ መሥራት እንደምንችል ማሳያ ናቸው ሲሉም ተናግረዋል።

በቀጣይም ትልልቅ የባቡርና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ለመገንባት ሰፊ ዕቅድ መያዙን ጨምረው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.