🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦ በዓድዋ ድል የታየውን አርበኝነት፣ የባቡር መሰረተ ልማት ስራዎችን በራስ አቅም በፍጥነትና በውጤታማነት በማጠናቀቅ ደግመን እናሳያለን ሲሉ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለጹ።
ከዐድዋ ተራሮች እስከ ጉባ፤ ዐድዋ በልኩ ሲዘከር!
የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር 130ኛውን የዓድዋ ድል በዓል አክብሯል።
በዓሉን በማስመልከት በራስ አቅም እየተገነባና እየተጠናቀቀ የሚገኘው የኤ.ኤም.ጂ ኢንዱስትሪ ፓርክን ከኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር የሚያገናኘው የሶስት ኪሎ ሜትር የባቡር መሰረተ ልማት ተጎብኝቷል።

በጉብኝቱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ፣ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ኢንጂነር ታከለ ኡማ ፤ አባቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነት ታላቁን የዓድዋ ድል ታሪክ አስረክበውናል ብለዋል።

እኛ ደግሞ ለቀጣዩ ትውልድ ስንቅ የሚሆን አኩሪ የባቡር ትራንስፖርት መሠረት ልማት በራስ አቅም እየገነባን እንገኛለን ብለዋል።
እየተገነቡ የሚገኙት የባቡር መሰረተ ልማቶች ነገ ላይ ከዚህ የተሻለና የበለጠ ሥራ መሥራት እንደምንችል ማሳያ ናቸው ሲሉም ተናግረዋል።
በቀጣይም ትልልቅ የባቡርና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ለመገንባት ሰፊ ዕቅድ መያዙን ጨምረው ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026