🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦ በዓድዋ ድል የታየውን አርበኝነት፣ የባቡር መሰረተ ልማት ስራዎችን በራስ አቅም በፍጥነትና በውጤታማነት በማጠናቀቅ ደግመን እናሳያለን ሲሉ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለጹ።
ከዐድዋ ተራሮች እስከ ጉባ፤ ዐድዋ በልኩ ሲዘከር!
የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር 130ኛውን የዓድዋ ድል በዓል አክብሯል።
በዓሉን በማስመልከት በራስ አቅም እየተገነባና እየተጠናቀቀ የሚገኘው የኤ.ኤም.ጂ ኢንዱስትሪ ፓርክን ከኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር የሚያገናኘው የሶስት ኪሎ ሜትር የባቡር መሰረተ ልማት ተጎብኝቷል።

በጉብኝቱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ፣ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ኢንጂነር ታከለ ኡማ ፤ አባቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነት ታላቁን የዓድዋ ድል ታሪክ አስረክበውናል ብለዋል።

እኛ ደግሞ ለቀጣዩ ትውልድ ስንቅ የሚሆን አኩሪ የባቡር ትራንስፖርት መሠረት ልማት በራስ አቅም እየገነባን እንገኛለን ብለዋል።
እየተገነቡ የሚገኙት የባቡር መሰረተ ልማቶች ነገ ላይ ከዚህ የተሻለና የበለጠ ሥራ መሥራት እንደምንችል ማሳያ ናቸው ሲሉም ተናግረዋል።
በቀጣይም ትልልቅ የባቡርና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ለመገንባት ሰፊ ዕቅድ መያዙን ጨምረው ገልጸዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025