🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦ በዓድዋ ድል የታየውን አርበኝነት፣ የባቡር መሰረተ ልማት ስራዎችን በራስ አቅም በፍጥነትና በውጤታማነት በማጠናቀቅ ደግመን እናሳያለን ሲሉ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለጹ።
ከዐድዋ ተራሮች እስከ ጉባ፤ ዐድዋ በልኩ ሲዘከር!
የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር 130ኛውን የዓድዋ ድል በዓል አክብሯል።
በዓሉን በማስመልከት በራስ አቅም እየተገነባና እየተጠናቀቀ የሚገኘው የኤ.ኤም.ጂ ኢንዱስትሪ ፓርክን ከኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር የሚያገናኘው የሶስት ኪሎ ሜትር የባቡር መሰረተ ልማት ተጎብኝቷል።

በጉብኝቱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ፣ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ኢንጂነር ታከለ ኡማ ፤ አባቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነት ታላቁን የዓድዋ ድል ታሪክ አስረክበውናል ብለዋል።

እኛ ደግሞ ለቀጣዩ ትውልድ ስንቅ የሚሆን አኩሪ የባቡር ትራንስፖርት መሠረት ልማት በራስ አቅም እየገነባን እንገኛለን ብለዋል።
እየተገነቡ የሚገኙት የባቡር መሰረተ ልማቶች ነገ ላይ ከዚህ የተሻለና የበለጠ ሥራ መሥራት እንደምንችል ማሳያ ናቸው ሲሉም ተናግረዋል።
በቀጣይም ትልልቅ የባቡርና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ለመገንባት ሰፊ ዕቅድ መያዙን ጨምረው ገልጸዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026