🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦የዓድዋ ድል ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነፃነት ፋና ወጊ ከመሆኑም ባለፈ በልማት ሥራዎች ታሪክን ለመድገም ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥር መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ ገለጹ።
በኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል ተክብሯል።
በዓድዋ ድል የታየውን አርበኝነት፣ የባቡር መሰረተ ልማትን በራስ አቅም በውጤታማነት በመገንባት እንደግመዋለን
ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ በዚሁ ወቅት፤ የዓድዋ ድል ለፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ መሠረት የጣለ ታላቅ ድል ነው ብለዋል።

የአሁኑ ትውልድ የአባቶቹን አርበኝነት በልማት ሥራዎች ሊደግመው እንደሚገባ ጠቁመው አሁን ላይ ድህነትን ታሪክ ለማድረግ በጋራ መረባረብ ይገባል ብለዋል፡፡
በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ የልማት ሥራዎች የሀገሪቱን ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸውንም አብራርተዋል።
በተለይም በባቡር መሰረተ ልማት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አስደናቂ የአርበኝነት ሥራ መሆናቸውን ጠቅሰው ዘርፉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ትስስር ትልቅ መሠረት እየጣለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ሠራተኞች በቁርጠኝነትና በከፍተኛ መነሳሳት እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025