🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦የዓድዋ ድል ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነፃነት ፋና ወጊ ከመሆኑም ባለፈ በልማት ሥራዎች ታሪክን ለመድገም ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥር መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ ገለጹ።
በኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል ተክብሯል።
በዓድዋ ድል የታየውን አርበኝነት፣ የባቡር መሰረተ ልማትን በራስ አቅም በውጤታማነት በመገንባት እንደግመዋለን
ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ በዚሁ ወቅት፤ የዓድዋ ድል ለፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ መሠረት የጣለ ታላቅ ድል ነው ብለዋል።

የአሁኑ ትውልድ የአባቶቹን አርበኝነት በልማት ሥራዎች ሊደግመው እንደሚገባ ጠቁመው አሁን ላይ ድህነትን ታሪክ ለማድረግ በጋራ መረባረብ ይገባል ብለዋል፡፡
በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ የልማት ሥራዎች የሀገሪቱን ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸውንም አብራርተዋል።
በተለይም በባቡር መሰረተ ልማት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አስደናቂ የአርበኝነት ሥራ መሆናቸውን ጠቅሰው ዘርፉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ትስስር ትልቅ መሠረት እየጣለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ሠራተኞች በቁርጠኝነትና በከፍተኛ መነሳሳት እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026