የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የዓድዋ ድል በልማት ሥራዎች ታሪክን ለመድገም ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥር ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦የዓድዋ ድል ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነፃነት ፋና ወጊ ከመሆኑም ባለፈ በልማት ሥራዎች ታሪክን ለመድገም ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥር መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ ገለጹ።

በኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል ተክብሯል።

በዓድዋ ድል የታየውን አርበኝነት፣ የባቡር መሰረተ ልማትን በራስ አቅም በውጤታማነት በመገንባት እንደግመዋለን

ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ በዚሁ ወቅት፤ የዓድዋ ድል ለፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ መሠረት የጣለ ታላቅ ድል ነው ብለዋል።


የአሁኑ ትውልድ የአባቶቹን አርበኝነት በልማት ሥራዎች ሊደግመው እንደሚገባ ጠቁመው አሁን ላይ ድህነትን ታሪክ ለማድረግ በጋራ መረባረብ ይገባል ብለዋል፡፡

በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ የልማት ሥራዎች የሀገሪቱን ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸውንም አብራርተዋል።

በተለይም በባቡር መሰረተ ልማት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አስደናቂ የአርበኝነት ሥራ መሆናቸውን ጠቅሰው ዘርፉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ትስስር ትልቅ መሠረት እየጣለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ሠራተኞች በቁርጠኝነትና በከፍተኛ መነሳሳት እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026