የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ማዕከሉ በተቋቋመ ስድስት ወራት ውስጥ ከ23 ሺህ በላይ ሰዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት አግኝተዋል

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬደዋ፣ የካቲት 26/2018(ኢዜአ) :-የድሬዳዋ መሶብ የአንድ ማዕከል በተቋቋመ ስድስት ወራት ውስጥ ከ23 ሺህ በላይ ሰዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸው ተገለጸ።

የማዕከሉ አስተባባሪ አቶ አወቀ ለገሰ ለኢዜአ እንደገለጹት በመስከረም 2018 ስራ የጀመረው ማእከሉ በ10 ተቋማት 28 አገልግሎቶች እየተሰጡ ነው።

ማእከሉ ስራ ከጀመረ ወዲህ ከ23ሺህ በላይ ሰዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።


ማእከሉ ከወረቀት ንክኪ የፀዳ ዘመናዊ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህዝብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

በተሰራው የእርካታ ዳሰሳ ጥናት ህብረተሰቡ በመንግስት አገልግሎት ከፍተኛ እርካታ ማግኘት እንደቻለ መረጋገጡን አመልክተዋል።

በማዕከሉ የተሰባሰቡ ተቋማት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ ተገልጋዮች ናቸው።

ከተገልጋዮች መካከል አቶ አብዲ ቡሽራ እንዳሉት በማዕከሉ የሚሰጡት ዲጂታል አገልግሎቶች አስደሳች መሆናቸውን ገልጸዋል።


በማዕከሉ የይዞታ ካርታ ለማውጣት መጥተው ፈጣን አገልግሎት በማግኘታቸው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ አጠናቀው ወደ ስራቸው መመለስ እንደቻሉ ተናግረዋል።

ቀደም ሲል ተቋማት በተለያዩ አካባቢዎች ተበታትነው ስለሚገኙ አንድ አገልግሎት ለማግኘት እስከ ሳምንት ጊዜ እንደሚፈጅና ብዙ ድካም ይጠይቅ እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ በመጣው ለውጥ መደሰታቸውን ገልጸዋል።


ወይዘሮ ሰላማዊት ሐጎስ በበኩላቸው ግብር ለመክፈል ወደ ማእከሉ መምጣታቸውን ጠቁመው ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ መጨረሳቸውን ተናግረዋል ።

ወደ ማእከሉ ጉዳይ ለማስፈጸም መጥተው ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ አቶ ፍሰሐ ሰለሞን ናቸው።


በማእከሉ ተቋማት በሚሰጡት ፈጣን አገልግሎት መደሰታቸውን ጠቁመው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.