🔇Unmute
አሶሳ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግልገል በለስ ከተማ የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አሳዬ አበበ ተናገሩ።
የኮሪደር ልማት ከተሞችን ከማዘመን ባለፈ ለኑሮና ለንግድ አመቺ እንዲሆኑ አስችሏቸዋል።

ልማቱ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በመላ የሀገሪቱ ከተሞች በመስፋት የከተሞቹን ገጽታ በእጅጉ እየለወጠ ይገኛል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማን ጨምሮ በባምባሲ እና ግልገል በለስ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ግልገል በለስ ከተማ 3 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ከተጀመረ ሁለት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ግንባታው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አሳዬ አበበ ለኢዜአ ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ በመቀየር ለነዋሪዎቿ እና ለጎብኚዎች ተመራጭ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
ከተማዋ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መዳረሻ በመሆኗ የኮሪደር ልማቱ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን አካቶ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።
የአረንጓዴ ቦታዎች፣ የህዝብ መጸዳጃ ቤት፣ ካፍቴሪያና የመዝናኛ ማዕከላትን የያዘው የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
አሁኑ ላይ የእግረኞች እና የብስክሌት መንገድ በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነና የአገልግሎት መስጫ ማዕከላቱንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የከተማዋ ነዋሪዎች የኮሪደር ልማቱን በጉልበት እና በገንዘብ መደገፋቸውን ጠቁመው፤ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ከንቲባው ጠይቀዋል።
የኮሪደር ልማቱ በፍጥነት እና በጥራት እንዲከናወን አመራሩ የቅርብ ክትትል እያደረገ መሆኑንም ጨምረው አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025