የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የግልገል በለስ ከተማ የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግልገል በለስ ከተማ የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አሳዬ አበበ ተናገሩ።

የኮሪደር ልማት ከተሞችን ከማዘመን ባለፈ ለኑሮና ለንግድ አመቺ እንዲሆኑ አስችሏቸዋል።


ልማቱ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በመላ የሀገሪቱ ከተሞች በመስፋት የከተሞቹን ገጽታ በእጅጉ እየለወጠ ይገኛል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማን ጨምሮ በባምባሲ እና ግልገል በለስ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።


ግልገል በለስ ከተማ 3 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ከተጀመረ ሁለት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ግንባታው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አሳዬ አበበ ለኢዜአ ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ በመቀየር ለነዋሪዎቿ እና ለጎብኚዎች ተመራጭ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።

ከተማዋ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መዳረሻ በመሆኗ የኮሪደር ልማቱ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን አካቶ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።

የአረንጓዴ ቦታዎች፣ የህዝብ መጸዳጃ ቤት፣ ካፍቴሪያና የመዝናኛ ማዕከላትን የያዘው የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

አሁኑ ላይ የእግረኞች እና የብስክሌት መንገድ በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነና የአገልግሎት መስጫ ማዕከላቱንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የከተማዋ ነዋሪዎች የኮሪደር ልማቱን በጉልበት እና በገንዘብ መደገፋቸውን ጠቁመው፤ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ከንቲባው ጠይቀዋል።

የኮሪደር ልማቱ በፍጥነት እና በጥራት እንዲከናወን አመራሩ የቅርብ ክትትል እያደረገ መሆኑንም ጨምረው አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026