የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የግልገል በለስ ከተማ የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግልገል በለስ ከተማ የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አሳዬ አበበ ተናገሩ።

የኮሪደር ልማት ከተሞችን ከማዘመን ባለፈ ለኑሮና ለንግድ አመቺ እንዲሆኑ አስችሏቸዋል።


ልማቱ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በመላ የሀገሪቱ ከተሞች በመስፋት የከተሞቹን ገጽታ በእጅጉ እየለወጠ ይገኛል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማን ጨምሮ በባምባሲ እና ግልገል በለስ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።


ግልገል በለስ ከተማ 3 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ከተጀመረ ሁለት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ግንባታው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አሳዬ አበበ ለኢዜአ ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ በመቀየር ለነዋሪዎቿ እና ለጎብኚዎች ተመራጭ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።

ከተማዋ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መዳረሻ በመሆኗ የኮሪደር ልማቱ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን አካቶ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።

የአረንጓዴ ቦታዎች፣ የህዝብ መጸዳጃ ቤት፣ ካፍቴሪያና የመዝናኛ ማዕከላትን የያዘው የኮሪደር ልማት በፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

አሁኑ ላይ የእግረኞች እና የብስክሌት መንገድ በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነና የአገልግሎት መስጫ ማዕከላቱንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የከተማዋ ነዋሪዎች የኮሪደር ልማቱን በጉልበት እና በገንዘብ መደገፋቸውን ጠቁመው፤ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ከንቲባው ጠይቀዋል።

የኮሪደር ልማቱ በፍጥነት እና በጥራት እንዲከናወን አመራሩ የቅርብ ክትትል እያደረገ መሆኑንም ጨምረው አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026