የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች እየተሰራጨ ነው

Mar 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ለ2018/2019 የምርት ዘመን የሚውል ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ዘመናዊ ማዳበሪያ ወደ ዞኑ ገብቶ ለአርሶ አደሮች እየተሰራጨ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው የግብዓት አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ ኃይለኢየሱስ ዳምጤ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዞኑ ትርፍ አምራች በመሆኑ ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦቱ ቀድሞ እንዲከናወን እየተደረገ ነው።

በዚህም ለመጪው የምርት ዘመን በአጠቃላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ ሥራዎች ተጀምረዋል።

እስካሁን በተደረገው ጥረትም ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ወደ ዞኑ የገባ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በመሠረታዊ ማኅበራት በኩል ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ገልጸዋል።

ይህም በምርት ዘመኑ በእቅድ የተያዘውን 25 ሚሊዮን ኩንታል የምርት ግብ ለማሳካት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.