🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ለ2018/2019 የምርት ዘመን የሚውል ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ዘመናዊ ማዳበሪያ ወደ ዞኑ ገብቶ ለአርሶ አደሮች እየተሰራጨ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው የግብዓት አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ ኃይለኢየሱስ ዳምጤ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዞኑ ትርፍ አምራች በመሆኑ ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦቱ ቀድሞ እንዲከናወን እየተደረገ ነው።
በዚህም ለመጪው የምርት ዘመን በአጠቃላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ ሥራዎች ተጀምረዋል።
እስካሁን በተደረገው ጥረትም ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ወደ ዞኑ የገባ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በመሠረታዊ ማኅበራት በኩል ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ገልጸዋል።
ይህም በምርት ዘመኑ በእቅድ የተያዘውን 25 ሚሊዮን ኩንታል የምርት ግብ ለማሳካት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026