🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ለ2018/2019 የምርት ዘመን የሚውል ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ዘመናዊ ማዳበሪያ ወደ ዞኑ ገብቶ ለአርሶ አደሮች እየተሰራጨ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው የግብዓት አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ ኃይለኢየሱስ ዳምጤ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዞኑ ትርፍ አምራች በመሆኑ ምርታማነትን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦቱ ቀድሞ እንዲከናወን እየተደረገ ነው።
በዚህም ለመጪው የምርት ዘመን በአጠቃላይ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ ሥራዎች ተጀምረዋል።
እስካሁን በተደረገው ጥረትም ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ወደ ዞኑ የገባ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በመሠረታዊ ማኅበራት በኩል ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ገልጸዋል።
ይህም በምርት ዘመኑ በእቅድ የተያዘውን 25 ሚሊዮን ኩንታል የምርት ግብ ለማሳካት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025