የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ጣልያን በማቴይ እቅድ የኢትዮጵያን ስትራቴጂካዊ መሰረተ ልማቶች ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን ገለጸች

Mar 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9 /2018 (ኢዜአ)፦ ጣልያን የኮይሻ ኃይል ማመንጫን ጨምሮ በማቴይ እቅድ (Mattei Plan) የኢትዮጵያን ስትራቴጂካዊ መሰረተ ልማቶች ለመደገፍ ጽኑ ፍላጎት እና ቁርጠኝነት እንዳላት አስታወቀች።

በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የተመራው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በስትራቴጂካዊ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ዙሪያ ከጣልያኑ የማቴይ ዕቅድ (Mattei Plan) ግብረ ኃይል ጋር በሮም ውይይት አድርጓል።

ውይይቱ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማሳደግ ያለመ ሲሆን በኢትዮጵያ የልማት አጀንዳ ውስጥ ቁልፍ ድርሻ ባላቸው ትላልቅ ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት አድርጓል።

ፕሮጀክቶቹ የኮይሻ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ የግንባታ ፕሮጀክት እና የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ልማት ናቸው።


እነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም እና የአቪዬሽን መሠረተ ልማት በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ለውጥ እንደሚያመጡና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን እንደሚደግፉ ታምኖበታል።

በውይይቱ ላይ የጣልያን ወገን በማቴይ እቅድ ጥላ ሥር ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጠናከር ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት ገልጿል።

ይህም ፈጠራ የታከለባቸው የፋይናንስ ዘዴዎችን በመጠቀም እና በመንግሥትና በግል ዘርፍ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ተግባራዊ እንደሚሆን ተመልክቷል።

በውይይቱ የተሳተፈው የጣልያን ግብረ ኃይል ከጣልያን የኢኮኖሚና ፋይናንስ ሚኒስቴር፣ ከውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር፣ የጣልያን የኤክስፖርት ክሬዲት ኤጀንሲ (SACE)፣ የጣልያን መንግስት የፋይናንስ ተቋም (CDP) እና የጣልያኑ የግንባታ ኩባንያ ዊ ቢውልድ ግሩፕ (Webuild Group) የተወጣጡ ከፍተኛ ተወካዮችን ያካተተ ነው።

በውይይቱ ወቅት ሁለቱ ወገኖች ለኮይሻ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት የሚያስፈልገውን የፋይናንስ ዝግጅት፣ ተጨማሪ ሀብትን ማሰባሰብ እና የፋይናንስ መዋቅሩን ማሳለጥ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል።

በተጨማሪም ለቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የተቀናጀ የፋይናንስ አማራጮችን (blended finance) በመጠቀም የግል ዘርፉን ተሳትፎ ማሳደግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ሰፊ ሃሳብ ተለዋውጠዋል።


የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ፕሮጀክቶቹ በአገሪቱ እየተከናወነ ያለውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የረዥም ጊዜ የልማት ግቦችን ለመደገፍ ያላቸውን አስፈላጊነት አስገንዝበዋል።

ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ጣልያን ለኢትዮጵያ እያደረገች ላለው ቀጣይነት ያለው አጋርነት እና ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ሁለቱም ወገኖች የፕሮጀክቶቹን ግንባታ ለማፋጠን እና የተገቡ ቃሎችን ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር በቴክኒክ ረገድ በቅርበት አብሮ ለመሥራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026