የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ሀገሪቱን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ አድርጓታል 

Mar 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 10/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ሀገሪቱን ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከማድረግ ባለፈ፣ ኢኮኖሚዋን ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ መሆኑን የአንሞል ፕሮዳክትስ ጀነራል ማናጀር ራጂቭ ሻርማ ገለጹ።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ነጠላ የኢኮኖሚ አተያይን ወደ ብዝኅ ዘርፍ በማሸጋገር እመርታዊ ዕድገት እንዲመዘገብ እያስቻለ ነው

ጀነራል ማናጀሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤መንግስት የወሰዳቸው የማሻሻያ እርምጃዎች ለውጭ ባለሀብቶች የፈጠሩትን ምቹ ሁኔታ በዝርዝር አብራርተዋል።

በኢትዮጵያ የተፈጠረው ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ ለህንድ ባለሀብቶች ሰፊ ዕድል መፍጠሩን ጠቅሰው፤ በተለይም የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በቅርቡ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ትብብርን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል ብለዋል።

ሀገሪቱ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ቀደም ሲል ለውጭ ባለሀብቶች ዝግ የነበሩ የንግድ መስኮችን ክፍት ማድረጓ የኢንቨስትመንት አቅሟን በእጅጉ እንዳሳደገው ለአብነት ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ ሳቢ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እንድትሆን ያደረጓት ምክንያቶች በርካታ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በዚህም በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ ግዙፍ መሠረተ ልማቶች በተለይም በቅርቡ ግንባታው የተጀመረው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለንግድ እንቅስቃሴው ተጨማሪ ምቾት ይፈጥራል ብለዋል።

በሌላ መልኩ ሰፊ የሀገር ውስጥ ገበያ እና ከፍተኛ የምርትና አገልግሎት ፍላጎት መኖሩን ጠቁመው፤ ለኢንቨስትመንት ስራ ዝግጁ የሆነው ሰፊ ወጣት የሰው ኃይል ሌላው የሀገሪቱ ትልቅ አቅም መሆኑን አክለዋል፡፡

ባለሀብቶች ቪዛን፣ የሥራ ፈቃድንና ሌሎች አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በተሳለጠ መልኩ እንዲያገኙ መደረጉ የመንግስትን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይም ገልጸዋል።

በውጭ ምንዛሬ ረገድ የተወሰደው እርምጃም ጤናማ የገበያ ሁኔታን በመፍጠር ኢንቨስተሮች እኩል የውድድር ሜዳ እንዲያገኙና ተወዳዳሪ አቅም እንዲገነቡ ማስቻሉንም ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ ኢንቨስት በማድረግ ልምድ ያላቸው ነባር ባለሀብቶች የሀገሪቱን እምቅ አቅም ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026