🔇Unmute
ሀና፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኦሞ ዞን የቱሪስት መዳረሻዎችን በማልማት እና በማስተዋወቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የዞኑ አሥተዳደር ገለጸ።

ከተለያዩ መገናኛ ብዙኃን የተውጣጡ ባለሙያዎች በሳላማጎ፣ በበና ፀማይ ወረዳዎችና በቱርሚ ከተማ አሥተዳደር የሚገኙ መስኅቦችን ጎብኝተዋል።

የዞኑ አሥተዳደር የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ምኅረት አሳራቱ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የጉብኝቱ ዓላማ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማስተዋወቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ ነው።
በዞኑ የሚገኙ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ መስኅቦችን የማስተዋወቅ ሥራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ጠቅሰው፤ ካለው እምቅ ዐቅም አንጻር ገና ብዙ መሥራት እንደሚገባ አመላክተዋል።

ስለዚህ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማልማትና በማስተዋወቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሠራ ነው የተናገሩት።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026