የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ለዓመታት የተጓተቱ ፕሮጀክቶች ከወደቁበት እየተነሡ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Mar 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018 (ኢዜአ)፦ ለዓመታት የተጓተቱ ፕሮጀክቶች ከጠፉበት እየተመለሱ፤ ከወደቁበት እየተነሡ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የጎንደርን የውኃ ጥም ይቆርጣል፤ የገበሬውን መሬት ያጠጣል፤ የአካባቢውን ምኅዳር ይለውጣል የተባለው የመገጭ የመጠጥ ውኃ ግድብ የደረሰበትን ደረጃ መጎብኘታቸውን አመልክተዋል።

ለዓመታት የተጓተቱ ፕሮጀክቶች ከጠፉበት እየተመለሱ፤ ከወደቁበት እየተነሡ ነው ብለዋል።

የሀገር ሀብት ፈሶባቸው መክነው እና ባክነው የቀሩ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ከሞት እያስነሡ ማፋጠን የዚህ መንግሥት ልዩ መለያው መሆኑን ገልጸው የመገጭ ግድብ ደግሞ አስረጅ ምስክር እንደሆነ ተናግረዋል።

እሱ ራሱ የጀመራቸው ብቻ ሳይሆን ተጀምረው የውልደት ስብራት የገጠማቸው ፕሮጀክቶች በብልጽግና መንግሥት አዲስ እስትንፋስ እያገኙ ግንባታቸው እየተፋጠነ ይገኛል ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

“አቁሞ ያስቀርህ እንደ መገጭ ግድብ” የሚለው ቀርቶ የአካባቢው ሰው “ወድቀህ ተነሣ እንደ መገጭ ግድብ” ብሎ መተረት ጀምሯል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የብልጽግና መንግሥት ብሂል ያስቀይራል ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.