🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018 (ኢዜአ)፦ ለዓመታት የተጓተቱ ፕሮጀክቶች ከጠፉበት እየተመለሱ፤ ከወደቁበት እየተነሡ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የጎንደርን የውኃ ጥም ይቆርጣል፤ የገበሬውን መሬት ያጠጣል፤ የአካባቢውን ምኅዳር ይለውጣል የተባለው የመገጭ የመጠጥ ውኃ ግድብ የደረሰበትን ደረጃ መጎብኘታቸውን አመልክተዋል።

ለዓመታት የተጓተቱ ፕሮጀክቶች ከጠፉበት እየተመለሱ፤ ከወደቁበት እየተነሡ ነው ብለዋል።
የሀገር ሀብት ፈሶባቸው መክነው እና ባክነው የቀሩ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ከሞት እያስነሡ ማፋጠን የዚህ መንግሥት ልዩ መለያው መሆኑን ገልጸው የመገጭ ግድብ ደግሞ አስረጅ ምስክር እንደሆነ ተናግረዋል።
እሱ ራሱ የጀመራቸው ብቻ ሳይሆን ተጀምረው የውልደት ስብራት የገጠማቸው ፕሮጀክቶች በብልጽግና መንግሥት አዲስ እስትንፋስ እያገኙ ግንባታቸው እየተፋጠነ ይገኛል ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

“አቁሞ ያስቀርህ እንደ መገጭ ግድብ” የሚለው ቀርቶ የአካባቢው ሰው “ወድቀህ ተነሣ እንደ መገጭ ግድብ” ብሎ መተረት ጀምሯል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የብልጽግና መንግሥት ብሂል ያስቀይራል ሲሉ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025