የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የአዲስ አበባን የንግድና ኢንቨስትመንት ማዕከልነት የሚያጎለብት ዘመናዊ አሰራር ሥርዓት ተፈጥሯል 

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባን ዓለም አቀፍ የንግድና ኢንቨስትመንት ማዕከልነት የሚያጎለብት ዘመናዊ አሰራር ሥርዓት መፈጠሩን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በኢትዮጵያ እና በጣሊያን መካከል ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሯል

የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡


በመርሐ ግብሩ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጣሊያን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ምክትል ሚኒስትር ማሪያ ትሪፖዲ፣ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

በዚህ ወቅት የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ የመዲናዋ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ የልማት ስኬቶች ዓለም አቀፍ ተወዳዳረሪነትን በማሳደግ ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻነትን እያሳደገ ነው ብለዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የተወሰዱ ተጨባጭ የአገልግሎት አሰጣጥ የሪፎርም እርምጃዎችም ኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት የስበት ማዕከል እያደረጋት እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ የአዲስ መሶብ የዲጂታል የአንድ ማዕከልም አልሚ ባለሃብቶች የተሳለጠ የመንግስት አገልግሎት የሚያገኙበትን አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩን ተናግረዋል።

ይህም የአዲስ አበባን ፈጣን ዕድገት በማሳለጥ ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ካባቢን በመፍጠር የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ እያበረታታ መሆኑን አንስተዋል።

በንግድና ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚ ባለሃብቶች ድጋፍና ትብብር እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።


የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የሚያደርግ አመርቂ ውጤት እያስገኘ ነው ብለዋል።

ለአብነትም የሕዳሴ ግድብ ስኬት፣ አዲስ አበባን ጨምሮ ከ80 በላይ የከተሞች የኮሪደር ልማት ስኬቶች የኮንስትራክሽን ዘርፉን ፈጣን ዕድገት የሚያሳዩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ፈጣን ዕድገትም በሃብት ፈጠራና አስተዳደር ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮ-ጣሊያን የዲፕሎማሲ ወዳጅነት የጣሊያን ኩባንያዎች በግንባታ ግብዓት፣ ማሽነሪና መሰል የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበትን ዕድል እንደፈጠረ አብራርተዋል።

የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማትፎረምም የሀገራቱን ትብብር ወደላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026