የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በድሬዳዋ ገጠር ቀበሌዎች ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ ፤መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- በድሬዳዋ አስተዳደር ገጠር ቀበሌዎች ነዋሪዎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለማሸጋገር የተጀመሩ ውጤታማ ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል አመራሩ በቁርጠኝነት መትጋት እንዳለበት ተገለጸ።

በአስተዳደሩ በየደረጃው የሚገኙ የገጠር ክላስተር አመራሮችና ባለሙያዎች የተጀመሩ የበልግና የመኸር ግብርና ስራዎችን አጠናክረው በሚያስቀጥሉበት ጉዳይ ላይ ዛሬ ተወያይተዋል።


በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በዚሁ ወቅት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት አነስተኛ የመስኖ አውታሮችን ተደራሽ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተሠሩ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ፣ በሌማት ትሩፋትና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሮች አማካኝነት በርካቶች ከተረጂነት ወደ አምራችነት እየተሸጋገሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

በቀጣይም በአስተዳደሩ ገጠር ቀበሌዎች ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።


የአስተዳደሩ የግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በበኩላቸው፤ የመጠጥና የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ፣ የመስኖ ውሃ መሳቢያ ሞተሮች አቅርቦትና ሙያዊ ድጋፎች ለለውጡ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

በዘንድሮው ዓመት በሞዴልነት በአራቱ ክላስተሮች የሚተገበረው የገጠር ኮሪደር ልማት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸው፣ ይህም ለፍራፍሬና ለጥላ ችግኞች ልማት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር አመልክተዋል።

በመድረኩ ላይ አሁን እየጣለ የሚገኘውን የበልግ ዝናብ በአግባቡ በመጠቀም ለመኸር እርሻ አስፈላጊው ዝግጅት በወቅቱ መጠናቀቅ እንዳለበት አቅጣጫ ተቀምጧል።

በውይይቱ የተሳተፉ የገጠር ክላስተርና ቀበሌ አመራሮች በበኩላቸው፤ የተጀመሩ የልማት ኢኒሼቲቮችና የታቀደውን የኮሪደር ልማት ስኬታማ ለማድረግ በቅንጅትና በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026