🔇Unmute
ሆሳዕና፤መጋቢት16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ሁላችንም ሃላፊነት ወስደን በዘላቂነት እንሰራለን ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ።
በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራሮች፤ ኢትዮጵያ ተዘግቶባት ልትኖር የማትችል በመሆኑ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋ ምላሽ እንዲያገኝ የሁላችንም ሃላፊነት ሆኖ እንሰራለን ብለዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢዜማ ሰብሳቢ እና በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ደምስ ገብሬ፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ከብሄራዊ ጥቅምም ባለፈ የሀገርና የዜጎች የህልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ፓርቲያቸው የጸና አቋም ያለው መሆኑን አረጋግጠው በጋራ ምክር ቤቱም ለሀገር ብሄራዊ ጥቅም ተቀራርበን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ በረከት ከድር፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ከጥቅም ባለፈ የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም ይህንን የትውልድ ጥያቄ ሆኖ እየተነሳ ያለ ጉዳይ ምላሽ እንዲያገኝ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም አጀንዳ አድርጎ እየሰራበት መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ሁላችንም ሃላፊነት ወስደን በዘላቂነት እንሰራለን ሲሉ አረጋግጠዋል።

ያጋራ ምክር ቤቱ አባልና የጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ (ጎጎት) አመራር የሆኑት አብድልአዚዝ ሙሰማ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የዚህ ትውልድ የጋራ አጀንዳ በመሆኑ ለምላሹ በጋራ ቆመን እንሰራለን ብለዋል።
በዚህ ረገድ ፓርቲያቸው ጠንካራ አቋም ያለው መሆኑን አረጋግጠው ለሀገር ህልውና እና ብሄራዊ ጥቅም መሳካት ትብብርና አብሮነታቸን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ የታሪክ፣ የመልከአ ምድር እና ዓለም አቀፍ ህጎችን መሰረት ያደረገ ተገቢ ጥያቄ መሆኑ ይታወቃል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025