🔇Unmute
አምቦ፣ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሸዋ ዞን በዘንድሮ የበጋ መስኖ ልማት በመጀመሪያ ዙር ከለማው መሬት ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በጽህፈት ቤቱ የመስኖ ልማት ባለሙያ አቶ ገዛኸኝ ዲንሳ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በዞኑ በመስኖ የሚለማ መሬትን በማስፋት ምርትና ምርታማነትን በመጨመር የተሻለ ውጤት እየተገኘ ነው።

በዘንድሮ የበጋ መስኖ ልማት በአንደኛው ዙር 30 ሺህ ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ከእቅድ በላይ 32 ሺህ ሄክታር በተለያዩ የሰብል አይነቶች፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ማልማት ተችሏል ብለዋል።
በልማቱም ከ31 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ በመስኖ እየለማ ካለው መሬት ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡
የተሰበሰበው ምርት ገበያን በማረጋጋት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም ሁለተኛው ዙር የበጋ መስኖ ልማት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል።

በሁለተኛው ዙር የመስኖ ልማት ስራም ከ22 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በማልማት 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል የአትክልት ምርት ለመሰብሰብ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በመስኖ ልማቱ ከተሳተፉት መካከል የቶኬ ኩታዬ ወረዳ አርሶ አደር ተሾመ በቀለ፤ በዘመናዊ የመስኖ ልማት ታግዘው ማልማት ከጀመሩ ወዲህ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
ዘንድሮም የተሻለ ዝግጅት አድርገው እያለሙ መሆኑን አንስተው፣ ካለፈው የበለጠ ምርት እንደሚጠብቁ ነው የተናገሩት።
የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር ተፈራ በንቲ በበኩላቸው፤ በበጋ መስኖ ልማት ያገኙት ምርት ከፍጆታቸው አልፎ ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያቸውን እያሳደጉ መሆኑን ገልፀዋል።
በዞኑ ባለፈው ዓመት በአንደኛውና በሁለተኛው ዙር በመስኖ ከለማው መሬት 10 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱም ታውቋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025