የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምዕራብ ጎንደር ዞን በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 80 በርሜል ነዳጅ በቁጥጥር ስር ዋለ

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፣ መጋቢት18/2018 (ኢዜአ):-በምዕራብ ጎንደር ዞን በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 80 በርሜል ነዳጅ ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡

ነዳጁን መያዝ የተቻለው በምእራብ አርማጭሆ ወረዳ በሁለት አይሱዙ ተሽከርካሪ ተጭኖ በመጓጓዝ ላይ እያለ ነው።

በዚህም ፖሊስ 80 በርሜል ነዳጅ ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም በአቋራጭ ለመክበርና ለህገ ወጥ ዓላማ ለማዋል በማለም በሀገርና ህዝብ ላይ ተጨማሪ ጫና ለመፍጠር የተሞከረ ህገወጥ ተግባር መሆኑን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ምስጋናው ካሴ አብራርተዋል።

እንደዚህ አይነት ወንጀሎችን ለመከላከል የፀጥታ አካላት ባደረጉት ጠንካራ ፍተሻና በህብረተሰቡ ጥቆማ መሰረት በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረው ነዳጅ መያዙን ተናግረዋል።

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026