የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኮደርስ ስልጠና ዲጂታል የፈጠራ ስራዎችን ለማሳደግ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ዲጂታል የስራ ፈጠራ እድሎችን እና የፈጠራ ስራዎችን በማስፋት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን እያሳደገ መሆኑን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአምስት ሚሊየን የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና በተለይም ወጣቶች የእድሉ ተጠቃሚ ሆነው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ዜጎች ስልጠናውን እየወሰዱ ከራሳቸው አልፈው ለሀገራቸው የዲጂታል ልማት ስትራቴጂ ትግበራ አሻራቸውን እያኖሩ ይገኛሉ።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ስልጠናው የዜጎችን ዲጂታል ክህሎት በማሳደግ የአኗኗር ዘይቤን የሚያሳልጡ ክህሎቶችን ለማጎልበት ያስችላል።

በቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች ያላቸውን ክህሎት በማሳደግ ወደ ፈጠራ ስራዎች እንዲሸጋገሩ እገዛ አድርጓል ብለዋል።

ይህም የሀገሪቱን ተወዳዳሪነት በማሳደግ ወደ እውቀት መር ኢኮኖሚ ለሚደረገው ሽግግር አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

በትምህርት፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝምና ሌሎች ዘርፎች በዲጂታል ስርዓት እንዲታገዙ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል።


በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የአይ ሲቲ ዳይሬክተር ናኦል አንበሴ በበኩላቸው፤ በኢንስቲትዩቱ ተማሪዎችና ሰራተኞች ስልጠናውን እንዲወስዱ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ተጨማሪ ክህሎትን ለማጎልበት የሚረዳ በመሆኑ ዜጎች እድሉን በአግባቡ ሊጠቀሙበት ይገባል ብለዋል።


የአይሲ ቲ ባለሙያዋ ጥሩ መልካም ስልጠናው በየትኛውም ሙያ የተሰማሩ ዜጎች ስራቸውን ለማሻሻል ያለውን ሚና ገልጻለች።


ተማሪ ባዩሽ ተስፋዬ እና ከደቡብ ሱዳን የትምህርት ስኮላርሺፕ ተጠቃሚ የሆነው ላዱሊ ሞሪ ስልጠናው ከዲጂታል ዘመን ጋር አብሮ ለመራመድ ክህሎትን ለማሳደግ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.