የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ።

በከተሞቹ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን አስተማማኝ ለማድረግ የዲስትሪቡሽን መስመር መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት በመከናወን ላይ ይገኛል።

ፕሮጀክቱ የኃይል ማከፋፈያ ኔትወርክ ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዙ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚወጡ መስመሮችን መልሶ መገንባትና ማሻሻል፤ እንዲሁም ከፈቃድ በላይ የሆነ የኃይል ፍጆታን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ 62 የሎድ ብሬክ ስዊቾችን መግጠምን ያካትታል።

የሚገነቡት መስመሮች በኮንክሪት ምሰሶዎች እና በሽፍን ኬብል የሚከናወኑ በመሆናቸው ለአደጋ የማይጋለጡና ለረጅም ዓመታት አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ናቸው ተብሏል።

የአዲስ አበባ ዲስትሪቢውሽን ሪሃቢሊቴሽን 4ኛ ምዕራፍ ፕሮጀክት ሃላፊ ቅድስት ላቀው ለኢዜአ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ በዋናነት የኃይል ኔትወርክ እድሳትን እና የመስመሮችን አስተማማኝነት ማረጋገጥን ዓላማ ያደረገ ነው።

በዚህም 2 ሺህ አዲስ የተለያየ አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች ተከላና 2 ሺህ ነባር ትራንስፎርመሮች አቅም የማሳደግ ሥራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል፡፡

በፊዩዝ የነበረ ትራንስፎርመር ወጪ በዲስትሪቢዩሽን ቦክስ እንደሚሆን ተናግረው ይህም የሚቆራረጡ መስመሮች በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስ ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች 673 ኪሎሜትር የሚሆን መስመሮች እንደሚቀየሩ ገልጸው፤ ሽፋን የሌለው የኤሌክትሪክ መስመር ገመዶች እንደሚቀየሩና የኤሌክትሪክ መቆራረጥን እንደሚያስቀር ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ አስተማማኝ የሀይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል።


የቻይና ኢነርጂ ግሩፕ ምክትል ማናጀር ሁ ዊሚንግ ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎችን የማቆም ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ የማገናኘት እና የሙከራ ስራ መሆኑን ጠቁመዋል።


በፕሮጀክቱ የሎት አንድ ሳይት መሀንዲስ አረአያ ጌታሁን በምስራቅ ሪጅን ካሉ ሳይቶች ውስጥ ሶስቱ መጠናቀቃቸውን ገልጸው፤ በተያዘለት ጊዜ ማጠናቀቅ የሚያስችል ስራም እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026