🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ የታየውን የዋጋ ግሽበት ቅናሽ ዘላቂ ለማድረግ የጀመረውን ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ትግብራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።
የባንኩ ገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ዛሬ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን አድርጓል።
ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ፣ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በየካቲት ወር መጨረሻ ወደ 9 ነጥብ 7 በመቶ ዝቅ ማለቱን ገልጿል።

ምንም እንኳን የሀገር ውስጥ የዋጋ ግሽበት እየቀነሰ ቢሆንም፣ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ግጭት የነዳጅና የሸቀጦች ዋጋ መጨመር በኢኮኖሚው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊኖረው እንደሚችል አመልክቷል።
በዚህም ምክንያት ኮሚቴው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ (Tight Monetary Policy) መቀጠል እንዳለበት ወስኗል።
ብሔራዊ ባንኩ በሀገሪቱ እየታየ የመጣውን የዋጋ ግሽበት ቅናሽ አዝማሚያ ይበልጥ ለማረጋጋት፣ ባለፉት ወራት ሲተገብር የቆየውን ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

የባንኩ መነሻ ወለድ መጠን (NBR) ባለበት እንዲቀጥል እና ባንኮች ያላቸውን የቅሬታ ብድር (NPL) መጠን በመቀነስ የፋይናንስ ሥርዓቱ ጤናማነት እንዲጠበቅ አሳስቧል።
በተጨማሪም በመካከለኛው ምስራቅ ካለው ወቅታዊ ውጥረት ሊነሱ የሚችሉ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ስጋቶችን በንቃት መከታተል እንደሚያስፈልግም ነው የጠቆመው ኮሚቴው።

መንግስት የጀመረውን ጥንቃቄ የተሞላበት የበጀት አስተዳደር በማስቀጠል ከብሔራዊ ባንክ የሚወስደውን ቀጥተኛ ብድር እንዲያቆም እና የውጭ ምንዛሬ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በምክረ-ሐሳቡ አመልክቷል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025