የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር የያዘውን ጠንካራ የገንዘብ ፖሊሲ አቅጣጫ እንደሚቀጥል ገለጸ

Apr 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ የታየውን የዋጋ ግሽበት ቅናሽ ዘላቂ ለማድረግ የጀመረውን ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ትግብራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

የባንኩ ገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ዛሬ ስድስተኛ መደበኛ ስብሰባውን አድርጓል።

ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ፣ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በየካቲት ወር መጨረሻ ወደ 9 ነጥብ 7 በመቶ ዝቅ ማለቱን ገልጿል።


ምንም እንኳን የሀገር ውስጥ የዋጋ ግሽበት እየቀነሰ ቢሆንም፣ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ግጭት የነዳጅና የሸቀጦች ዋጋ መጨመር በኢኮኖሚው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊኖረው እንደሚችል አመልክቷል።

በዚህም ምክንያት ኮሚቴው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ (Tight Monetary Policy) መቀጠል እንዳለበት ወስኗል።

ብሔራዊ ባንኩ በሀገሪቱ እየታየ የመጣውን የዋጋ ግሽበት ቅናሽ አዝማሚያ ይበልጥ ለማረጋጋት፣ ባለፉት ወራት ሲተገብር የቆየውን ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።


የባንኩ መነሻ ወለድ መጠን (NBR) ባለበት እንዲቀጥል እና ባንኮች ያላቸውን የቅሬታ ብድር (NPL) መጠን በመቀነስ የፋይናንስ ሥርዓቱ ጤናማነት እንዲጠበቅ አሳስቧል።

በተጨማሪም በመካከለኛው ምስራቅ ካለው ወቅታዊ ውጥረት ሊነሱ የሚችሉ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ስጋቶችን በንቃት መከታተል እንደሚያስፈልግም ነው የጠቆመው ኮሚቴው።


መንግስት የጀመረውን ጥንቃቄ የተሞላበት የበጀት አስተዳደር በማስቀጠል ከብሔራዊ ባንክ የሚወስደውን ቀጥተኛ ብድር እንዲያቆም እና የውጭ ምንዛሬ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በምክረ-ሐሳቡ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026