🔇Unmute
አዲስ አበባ፤መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በጠንካራ የጥገና፣ እድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት ስኬታማ አየር መንገድ መፍጠር መቻሏን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለጹ።
በአዲስ አበባ ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአፍሪካ የጥገና፣ ዕድሳትና ኦፕሬሽን ኮንፍረንስ 2026 ዛሬ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ የተሟላ የጥገና፣ እድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት ስኬታማ አየር መንገድ መገንባት ያስችላል።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ የጥገና፣ ዕድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት ለብዙ ዓመታት ሰርቻለሁ ያሉት አቶ መስፍን ዘርፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስኬት ቁልፍ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስኬት ምስጢር በአየር መንገዱ ያለው የተሟላ የጥገና፣ ዕድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት መሆኑን ተናግረዋል።
በአፍሪካ የጥገና፣ዕድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት ክፍተት ያለበት በመሆኑ የአየር መንገዶችም ደካማ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአፍሪካ ጠንካራ የጥገና፣ዕድሳትና ኦፕሬሽን አገልግሎት ለመስጠት ሰፊ ሀብትና ዕውቀት ይፈልጋል ያሉት አቶ መስፍን፤ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የአፍሪካ አየር መንገዶች በትብብር መስራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
አፍሪካ ዕምቅ አቅም ያላቸው ወጣቶች እንዳሏት ገልጸው፤ወጣቶችን አሰልጥኖ ማሰማራት ይገባል ብለዋል።
በተለያዩ ዓለማት ካሉ የአየር መንገድ የጥገና፣ዕድሳትና ኦፕሬሽን ተቋማት ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025