🔇Unmute
አሶሳ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግስት የክልሉን የፖለቲካ ተሳትፎ ከማሳደግ ባለፈ በኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ዘርፎች አመርቂ ውጤት እንዲመዘገብ መሠረት መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር ተናገሩ።
መጋቢት 24 የለውጡ መንግስት የተሰጠውን ሀገራዊ ሀላፊነት በተመለከተ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ ለውጡ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ጅማሮ ማብሰሪያ እንደነበር አስታውሰዋል።
ለውጡ በክልሎች መካከል የነበረውን የፖለቲካ ተሳትፎ የበላይነትና የበታችነት በማስቀረት ሁሉም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ የሚወስኑበት አውድ መፍጠሩን ገልጸዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከለውጡ በፊት በነበረው የዳር ፖለቲካ ተሳትፎ በሀገር ጉዳይ ላይ የመወሰን አቅም እንዳልነበረው ጠቁመው የለውጡ መንግስት በፈጠረው አሳታፊ የፖለቲካ ስርዓት ተጠቃሚ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከለውጡ መንግስት በፊት በነበረው ስርዓት ክልሉ የተፈጥሮ ሀብቱን በነፃነት መጠቀም እንዳይችል በመደረጉ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዳልነበረ አንስተዋል።
በአሁኑ ወቅት የለውጡ መንግስት በፈጠረው የብዝሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ እሳቤ ክልሉ በግብርና፣ በማዕድን ልማት እና በሌሎች ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ተናግረዋል።
የመደመር መንግስት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ የወሰዳቸው የመፍትሄ አማራጮች በውጤት የታጀቡ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ኢሳቅ፤ የተቋማት ግንባታም በማንኛውም ሁኔታ የማይበገሩ ሆነው እንዲቀረፁ መደረጉን አብራርተዋል።
ሀገራዊ ለውጡ ህብረብሔራዊ አንድነትንና የወል ትርክት ግንባታን በማጠናከር እንዲሁም አዳዲስ እሳቤዎችን በመተግበር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጠ መሆኑን አክለዋል።
የመደመር መንግስት የተለያዩ የልማት ኢንሼቲቮችን በመተግበር ህብረተሰቡ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ በአረንጓዴ አሻራና በስንዴ ልማት ለሌሎች ሀገራት ተሞክሮ የሚሆን ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026