🔇Unmute
አሶሳ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ የለውጡ መንግስት የክልሉን የፖለቲካ ተሳትፎ ከማሳደግ ባለፈ በኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ዘርፎች አመርቂ ውጤት እንዲመዘገብ መሠረት መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር ተናገሩ።
መጋቢት 24 የለውጡ መንግስት የተሰጠውን ሀገራዊ ሀላፊነት በተመለከተ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ ለውጡ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ጅማሮ ማብሰሪያ እንደነበር አስታውሰዋል።
ለውጡ በክልሎች መካከል የነበረውን የፖለቲካ ተሳትፎ የበላይነትና የበታችነት በማስቀረት ሁሉም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ የሚወስኑበት አውድ መፍጠሩን ገልጸዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከለውጡ በፊት በነበረው የዳር ፖለቲካ ተሳትፎ በሀገር ጉዳይ ላይ የመወሰን አቅም እንዳልነበረው ጠቁመው የለውጡ መንግስት በፈጠረው አሳታፊ የፖለቲካ ስርዓት ተጠቃሚ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከለውጡ መንግስት በፊት በነበረው ስርዓት ክልሉ የተፈጥሮ ሀብቱን በነፃነት መጠቀም እንዳይችል በመደረጉ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዳልነበረ አንስተዋል።
በአሁኑ ወቅት የለውጡ መንግስት በፈጠረው የብዝሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ እሳቤ ክልሉ በግብርና፣ በማዕድን ልማት እና በሌሎች ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ተናግረዋል።
የመደመር መንግስት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ የወሰዳቸው የመፍትሄ አማራጮች በውጤት የታጀቡ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ኢሳቅ፤ የተቋማት ግንባታም በማንኛውም ሁኔታ የማይበገሩ ሆነው እንዲቀረፁ መደረጉን አብራርተዋል።
ሀገራዊ ለውጡ ህብረብሔራዊ አንድነትንና የወል ትርክት ግንባታን በማጠናከር እንዲሁም አዳዲስ እሳቤዎችን በመተግበር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጠ መሆኑን አክለዋል።
የመደመር መንግስት የተለያዩ የልማት ኢንሼቲቮችን በመተግበር ህብረተሰቡ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ በአረንጓዴ አሻራና በስንዴ ልማት ለሌሎች ሀገራት ተሞክሮ የሚሆን ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025