የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያ በዓድዋ ድል ያሳየችውን አህጉራዊ ምሳሌነት ዛሬም በልማት እየደገመችው ነው-አፍሪካውያን

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በዓድዋ ድል ያሳየችውን አህጉራዊ ምሳሌነት ዛሬም በልማት እየደገመችው ነው ሲሉ የዓድዋ ድል መታሰቢያን የጎበኙ አፍሪካውያን ገለጹ።

ኢትዮጵያ የጀግንነት ታሪክ መፍለቂያ ሀገር መሆኗን በመጥቀስ፥ የዓድዋ ድል መታሰቢያ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያንና የመላው ጥቁር ሕዝቦች አኩሪ የታሪክ ዓምድ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት የተካሄደው የ16ኛው የአፍሪካ አደጋ ስጋት አቅም ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢትዮጵያና የአፍሪካውያን የጀግንነት የታሪክ ማህደር የሆነውን የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።


በጉብኝታቸውም የድል ታሪክ ምስክር የሆኑ ቅርሶችንና የጀግንነት አሻራዎችን የተመለከቱ ሲሆን፣ የድል መታሰቢያው ከሀገር ባለፈ ለአፍሪካ የሚተርፍ ትልቅ ትምህርት የያዘ መሆኑን ገልጸዋል።

የዓድዋ ድል ድህነትን ለማሸነፍና ለአፍሪካ ብልጽግና በትብብር ለመሥራት ትልቅ መነሳሳትን የሚፈጥር መሆኑንም ተናግረዋል።

ከጎብኚዎቹ መካከል ጅቡቲያዊው ኢሳም አብዱልሃኪም በሰጡት አስተያየት፤ ኢትዮጵያ የጀግንነት ታሪክ መፍለቂያ መሆኗን በሙዚየሙ ውስጥ ካየኋቸው ታሪኮች ተረድቻለሁ ብለዋል።

የዓድዋ ድል ኢትዮጵያውያን ሲተባበሩ ለየትኛውም ፈተና የማይበገሩ መሆናቸውን ያረጋገጠ ደማቅ አሻራ መሆኑንም ተናግረዋል።

ይህም ለሁሉም አፍሪካውያን የአይበገሬነትን ትምህርት የሚሰጥ ነው ብለዋል።

ከዛምቢያ የመጡት መሲ ችሉ በበኩላቸው፤ የዓድዋ ድል መታሰቢያ የጦርነት ድልን የሚዘክር ብቻ ሳይሆን በዚህ ዘመን ለልማት መትጋትን የሚያስተምርና ወኔ የሚያስታጥቅ እንደሆነ ጠቁመዋል።


አፍሪካውያን ከዓድዋ ደማቅ ታሪክ ተምረን ከተባበርን፤ ልክ እንደ ጦርነቱ ሁሉ ድህነትንም ድል ማድረግ እንችላለን ነው ያሉት።

በአዲስ አበባ የተመለከቱት ውበትና ዕድገትም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ያላትን ምሳሌነት በተግባር ማሳየቱን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ ሱዳናዊው እስማዔል አሊ፤ ዓድዋ ትክክለኛ የአመራር ብቃትና የሕዝብ ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።


ኢትዮጵያ በጥንቱ ጀግንነቷ ብቻ ሳይሆን ዛሬም እያስመዘገበቻቸው በሚገኙ የልማት ስኬቶች ለአፍሪካ አርዓያ ሆና ቀጥላለች ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026