የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ በአፋጣኝ ወደ ስራ ማስገባት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ውይይት አድርጓል።

ፕሮጀክቱ በአለም ቅርስነት የተመዘገበው የጀጎል አለም አቀፍ ቅርስን ለነዋሪውና ለጎብኚዎች የበለጠ ምቹ ለማድረግ የሚያግዝ ስለመሆኑ ተገልጿል።

በውይይቱ ላይም የ''ዳር ሀረር'' የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት የሀገር ኩራት ከሆነው የጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ታሪክና ይዘት ጋር በማጣጣምና የጀጎል ባህላዊ የግንባታ ጥበብን በተከተለ መልኩ እንደሚከናወን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።


የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' የመልሶ ማልማት ፕሮጀክትም በቅርሱ ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎችን ህይወት ለማሻሻል የሚያግዝ መሆኑ ተጠቅሷል።

ፕሮጀክቱ የህዝብን ተጠቃሚነት ከማሳደግም ባሻገር የሀረርን ከፍታ ለማረጋገጥ በሚሰሩ ስራዎች የጎላ ፋይዳ እንዳለው ነው የተመላከተው።

በፕሮጀክቱም ዘመናዊ አገልግሎት የሚሰጡ ታሪካዊ ይዘታቸውን የጠበቁ የቱሪስት ማረፊያዎች ይገነባሉ ተብሏል።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅም ሀረርን በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የቅርስ ቱሪዝም መዳረሻ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ቢሮው በመረጃው አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026

<p>የባቡር መንገደኞች በፋይዳ መታወቂያ የትኬት አገልግሎት የሚያገኙበት ስርዓት ተግባራዊ ሊሆን ነው</p>

አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...

Feb 24, 2025

<p>የትራንስፖርት ዘርፍ ተዋናዮችን የሚያገናኘው መተግበሪያ ይፋ ሆኗል</p>

አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...

Feb 12, 2025