🔇Unmute
ነገሌ ቦረና፤ሚያዝያ 6/ 2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን ቆላማ ወረዳዎች በዘንድሮው የበልግ አዝመራ ከ160 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።
ምስራቅ ቦረና ቆላማና ዝናብ አጠር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በብዛት የእንስሳት እርባታ የሚካሄድበት ቢሆንም፤ከመጋቢት 15 እስከ ሚያዝያ አጋማሽ ያለው ጊዜ ዋነኛው የበልግ ዝናብና የእርሻ ወቅት መሆኑ ተገልጿል።
በጽሕፈት ቤቱ የሰብል ልማትና ጥበቃ ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው የበልግ ወቅት 176 ሺህ 223 ሄክታር መሬት ታርሶ ለዘር ተዘጋጅቷል።
በዞኑ ሁሉም ወረዳዎች ለበልግ አዝመራ ከተዘጋጀው መሬት ውስጥ እስካሁን 160 ሺህ 539 ሄክታር የሚሆነው በአራት ዋና ዋና ሰብሎች መልማቱን ገልጸዋል።
በቆላማ ወረዳዎቹ የታረሰው መሬት በስንዴ፣ በጤፍ፣ በበቆሎና በቦለቄ ምርጥ ዘር እየለማ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በዚህ የበልግ አዝመራ 137 ሺህ 324 አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ፤ ከእነዚህም መካከል 20 ሺህ 297 ያህሉ ሴቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በዞኑ በበልግ አዝመራ ከሚለማው መሬት በአጠቃላይ ከ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026