የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምስራቅ ቦረና ዞን በበልግ አዝመራ ከ160 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነገሌ ቦረና፤ሚያዝያ 6/ 2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን ቆላማ ወረዳዎች በዘንድሮው የበልግ አዝመራ ከ160 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።

ምስራቅ ቦረና ቆላማና ዝናብ አጠር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በብዛት የእንስሳት እርባታ የሚካሄድበት ቢሆንም፤ከመጋቢት 15 እስከ ሚያዝያ አጋማሽ ያለው ጊዜ ዋነኛው የበልግ ዝናብና የእርሻ ወቅት መሆኑ ተገልጿል።

በጽሕፈት ቤቱ የሰብል ልማትና ጥበቃ ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው የበልግ ወቅት 176 ሺህ 223 ሄክታር መሬት ታርሶ ለዘር ተዘጋጅቷል።

በዞኑ ሁሉም ወረዳዎች ለበልግ አዝመራ ከተዘጋጀው መሬት ውስጥ እስካሁን 160 ሺህ 539 ሄክታር የሚሆነው በአራት ዋና ዋና ሰብሎች መልማቱን ገልጸዋል።

በቆላማ ወረዳዎቹ የታረሰው መሬት በስንዴ፣ በጤፍ፣ በበቆሎና በቦለቄ ምርጥ ዘር እየለማ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በዚህ የበልግ አዝመራ 137 ሺህ 324 አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ፤ ከእነዚህም መካከል 20 ሺህ 297 ያህሉ ሴቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዞኑ በበልግ አዝመራ ከሚለማው መሬት በአጠቃላይ ከ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026

<p>የባቡር መንገደኞች በፋይዳ መታወቂያ የትኬት አገልግሎት የሚያገኙበት ስርዓት ተግባራዊ ሊሆን ነው</p>

አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...

Feb 24, 2025

<p>የትራንስፖርት ዘርፍ ተዋናዮችን የሚያገናኘው መተግበሪያ ይፋ ሆኗል</p>

አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...

Feb 12, 2025