የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምስራቅ ቦረና ዞን በበልግ አዝመራ ከ160 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነገሌ ቦረና፤ሚያዝያ 6/ 2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን ቆላማ ወረዳዎች በዘንድሮው የበልግ አዝመራ ከ160 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።

ምስራቅ ቦረና ቆላማና ዝናብ አጠር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በብዛት የእንስሳት እርባታ የሚካሄድበት ቢሆንም፤ከመጋቢት 15 እስከ ሚያዝያ አጋማሽ ያለው ጊዜ ዋነኛው የበልግ ዝናብና የእርሻ ወቅት መሆኑ ተገልጿል።

በጽሕፈት ቤቱ የሰብል ልማትና ጥበቃ ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው የበልግ ወቅት 176 ሺህ 223 ሄክታር መሬት ታርሶ ለዘር ተዘጋጅቷል።

በዞኑ ሁሉም ወረዳዎች ለበልግ አዝመራ ከተዘጋጀው መሬት ውስጥ እስካሁን 160 ሺህ 539 ሄክታር የሚሆነው በአራት ዋና ዋና ሰብሎች መልማቱን ገልጸዋል።

በቆላማ ወረዳዎቹ የታረሰው መሬት በስንዴ፣ በጤፍ፣ በበቆሎና በቦለቄ ምርጥ ዘር እየለማ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በዚህ የበልግ አዝመራ 137 ሺህ 324 አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ፤ ከእነዚህም መካከል 20 ሺህ 297 ያህሉ ሴቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዞኑ በበልግ አዝመራ ከሚለማው መሬት በአጠቃላይ ከ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026