🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦የአማራ ክልልን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ለማሳካት ሁላችንም በቁጭት ልንሠራ ይገባል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
የአማራ ክልልን የግብርና ዘርፍ ወደ ዘመናዊ፣ ምርታማና ተወዳዳሪነት ለማሸጋገር የሚያስችል የ10 ዓመት የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ ዛሬ ይፋ ተደርጓል።

የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የአማራ ክልል ሰፊ የተፈጥሮ ሀብት፣ የእንስሳት ሀብትና ለግብርና አመቺ የሆኑ መሬትና ውሃ ቢኖረውም እስካሁን ባለው ሂደት ዘርፉ ወደኋላ ቀርቶ መቆየቱን አውስተዋል።
ዛሬ ይፋ የሆነው ፍኖተ ካርታ በክልሉ ውስጥ ያለውን የልማትና የለውጥ ፍላጎት ማስተሳሰሩን ጠቅሰው፤ ዕቅዱ ማህበረሰቡንና አመራሩን ወደ አንድ የጋራ ዓላማ ማምጣት መቻሉን እንደ ትልቅ ስኬት አንስተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፤ እንደ ሀገር በአምስቱ የብዝኃ ዘርፎች የታቀዱ ሥራዎች ውጤት እያመጡ መሆኑን አንስተዋል።
በአማራ ክልል ከሸዋ ሮቢት እስከ ቆቦና ዋግ መስመር እጅግ ሰፊ የአትክልትና ፍራፍሬ ክላስተር የመሆን አቅም እንዳለው በማንሳት፤ ይህን ማልማት ከሀገር ያለፈ አበርክቶ ይኖረዋል ብለዋል።
አርሶ አደሩ የሚጠቅመውን ነገር ካገኘ ለመተግበር ዝግጁ መሆኑን በማንሳት፤ የ10 ዓመቱን ፍኖተ ካርታ ወደ መሬት ማውረድ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ለዚህም ሁላችንም በቁጭት መነሳት አለብን ነው ያሉት።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ በበኩላቸው፤ ፍኖተ ካርታው የዜጎችን ሕይወት ለመቀየርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል።
ፍኖተ ካርታው አራት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ ያተኮረ መሆኑን በማንሳት፤ የተሻሻሉ ዝርያዎችን፣ ግብዓቶችንና ቴክኖሎጂን በመጠቀም በሰብልና በእንስሳት ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የእሴት ሰንሰለትና ኢንቨስትመንትን ማስፋት፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃን በማጎልበት የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ግብርና መገንባት እንዲሁም ተቋማዊ የመፈጸም አቅምን ማሳደግ ናቸው ብለዋል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሚኒስቴሩ የክልሎችን ጸጋ መሠረት ያደረገ የ10 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026