🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፋት ዘጠኝ ወራት ከወጪ ንግድ ከሰባት ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለፁ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ እያካሄደ ነው።
መድረኩ “ተወዳዳሪ የንግድ ሥርዓትና የተሳለጠ የገበያ ትስስር ለኢኮኖሚ ሽግግር” በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የተቋሙ ተልዕኮ የመፈጸም አቅሙ በየጊዜው እያደገ በመምጣቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም ዘርፎች አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል።
በዘጠኝ ወራቱ በኦንላይን ንግድ ምዝገባ፣አዲስ ፈቃድ የማውጣት፣ የማደስ እና መሰረዝ ሥራዎች ለሁለት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት መሰጠቱን ተናግረዋል።
በወጪ ንግድ ረገድ ከሁሉም የንግድ ዓይነቶች ሰባት ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የተገኘ መሆኑን አብራርተዋል።
የገበያ መሠረተ ልማት በማስፋት ረገድ ገበያ ለማረጋጋት የሚረዱ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ቁጥር በአሁኑ ወቅት 2ሺህ 190 መድረሱን ተናግረዋል።
ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ መጠናከሩን አንስተው፤ በዘጠኝ ወራት ሁለት ተመርቀው ወደ ሥራ መግባታቸውን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ሌሎች ሰባት ማዕከላት በግንባታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
በምርት ጥራትና ቁጥጥር ረገድ ተጨባጭ ለውጥ መመዝገቡን ገልፀው፤ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚመጥኑ ደረጃዎችን የማውጣትና የማስተዳደር ሥርዓት መዘርጋቱን ገልፀዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025