የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በሸገር ከተማ የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የበለጠ ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቷል

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚያዝያ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የበለጠ ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መገኘቱን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።

በሸገር ከተማ ያለውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን አስመልክቶ የመስክ ምልከታ እየተካሄደ ነው።

በመስክ ምልከታው ላይም የሸገር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጉዮ ገልገሎ እንደገለፁት፤ በሸገር ከተማ የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የበለጠ ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቷል።

ከተማዋ ከተመሰረተች በኋላ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች የህብረተሰቡን ህይወት የቀየሩ ከመሆናቸውም በላይ ኢኮኖሚያዊ ሽግግርን እውን ከማድረግ አኳያ ውጤቶች ተመዝግበዋል።

ከለውጡ በኋላ በከተማዋ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ፣ ዘመናዊ አገልግሎቶችን በማስፈን፣ ክህሎትን በማዳበር እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ ረገድ በተሰራው ስራ ውጤት መገኘቱን አክለዋል።


በኢንቨስትመንት ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ከመፍታትና አገልግሎት አሰጣጥን ከማዘመን ጎን ለጎን በከተማዋ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በምርምር በመለየት መሰራቱን አመልክተዋል።

የአርሶ አደሮችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከ ከ1 ሺህ 300 በላይ አርሶ አደሮች ክህሎታቸውን ለማጠናከር የሚያስችል ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል።

በዚህም መሰረት የኢንቨስትመንት እድገቱን ከተማው ከመመስረቱ በፊት ከነበረው በእጥፍ ማሳደግ መቻሉንም አስረድተዋል።

ባለፉት ሶስት ዓመታት የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብቶች፣ አርሶ አደሮችና ሌሎችን ጨምሮ አጠቃላይ 1 ሺህ 504 ኢንቨስትመንቶች 4 ሺህ 493 ሄክታር መሬትን ማልማት ችለዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026

<p>የባቡር መንገደኞች በፋይዳ መታወቂያ የትኬት አገልግሎት የሚያገኙበት ስርዓት ተግባራዊ ሊሆን ነው</p>

አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...

Feb 24, 2025