የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በአማራ ክልል የበልግ ወቅት እስካሁን ከ241 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያየ ሰብሎች እየለማ ነው

Apr 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ሚያዚያ 10/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የበልግ ወቅት እስካሁን ከ241 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያየ ሰብሎች መልማቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ምርታማነትን ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትንና የዘንድሮውን የበልግ ወቅት ልማት በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በማብራሪያቸውም የክልሉን የግብርና ዘርፍ በማዘመን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥና ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በያዘነው የበልግ ወቅት ከ245 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት መታቀዱን አስታውሰው እስካሁን ከ241 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያየ ሰብሎች መሸፈን ተችሏል ብለዋል።

አሁን እየጣለ ያለው የበልግ ዝናብ ለሰብል ልማት ተስማሚ በመሆኑ በተለይም የስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍ፣ ቦለቄ፣ ማሾ፣ አተር፣ ምስርና ሌሎችንም ሰብሎች መዝራት ስለመቻሉ ተናግረዋል።

የልማት ጥረቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን የገለጹት ዶ/ር ማንደፍሮ በበልጉ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የሰሜን ሽዋ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ ችሮታው አስፋው፤ በዞኑ ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የአካባቢውን ምቹነት መሰረት ያደረጉ የግብርና ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም የበልጉን ዝናብ በመጠቀም በዞኑ እስካሁን ከ86 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን ጠቅሰው ከዚህም ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት የሚገኝ ይሆናል ብለዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን የተሁለደሬ ወረዳ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋጨፋ ወረዳ የኢዜአ ሪፖርተር ያነጋገራቸው አርሶ አደሮች በዘንድሮው የበልግ ውቅት የእስካሁኑ እንቅስቃሴ ጥሩ መሆኑን አንስተው ከፍተኛ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026