የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ ይሰራል - አቶ ኦርዲን በድሪ

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ) ፦ በሀረር ከተማ የተጀመረውን ሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭ በጥራትና ፍጥነት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩና ካቢኔያቸው በክልሉ እየተገነባ የሚገኘው የሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።


በዚህ ወቅትም ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በአው ሀኪም ተራራ ላይ እየተሰራ የሚገኘው ኢኒሼቲቩ የአዲሲቷ ሀረር አለም አቀፍ ምልክት ከመሆን ባሻገር ለክልሉ የቱሪዝም ዘርፍ እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅም ለቱሪዝም መዳረሻነትና ለህዝብ መዝናኛነት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የፕሮጀክቱ እውን መሆን የጎብኚዎች ቆይታን በመጨመር ተጠቃሚነትን ከማሳደግ አንፃርም ሚናው ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።


በፕሮጀክቱም 1ሺህ 870 ደረጃዎች እና 2 ኪሎሜትር የሚጠጋ የመሰረተ ልማት ስራ እንደሚከናወን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ ፕሮጀክቱ አካባቢያዊ ሀብቶችን በመጠቀም ይሰራል ብለዋል።

ተራራው ራሱን የቻለ የህግ ማዕቀፍ እንዲኖረው በማድረግ ተገቢው ጥበቃ እንደሚደረግለት አመላክተው ለዚህም ህገ-ወጥ ግንባታን በመከላከል ረገድ በቅንጅት እንደሚሰራም ተናግረዋል።

ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ጠቁመው ለዚህም የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ሲሉ ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026

<p>የባቡር መንገደኞች በፋይዳ መታወቂያ የትኬት አገልግሎት የሚያገኙበት ስርዓት ተግባራዊ ሊሆን ነው</p>

አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...

Feb 24, 2025