🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤ ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ) ፦ በሀረር ከተማ የተጀመረውን ሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭ በጥራትና ፍጥነት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩና ካቢኔያቸው በክልሉ እየተገነባ የሚገኘው የሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

በዚህ ወቅትም ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በአው ሀኪም ተራራ ላይ እየተሰራ የሚገኘው ኢኒሼቲቩ የአዲሲቷ ሀረር አለም አቀፍ ምልክት ከመሆን ባሻገር ለክልሉ የቱሪዝም ዘርፍ እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅም ለቱሪዝም መዳረሻነትና ለህዝብ መዝናኛነት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም የፕሮጀክቱ እውን መሆን የጎብኚዎች ቆይታን በመጨመር ተጠቃሚነትን ከማሳደግ አንፃርም ሚናው ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።

በፕሮጀክቱም 1ሺህ 870 ደረጃዎች እና 2 ኪሎሜትር የሚጠጋ የመሰረተ ልማት ስራ እንደሚከናወን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ ፕሮጀክቱ አካባቢያዊ ሀብቶችን በመጠቀም ይሰራል ብለዋል።
ተራራው ራሱን የቻለ የህግ ማዕቀፍ እንዲኖረው በማድረግ ተገቢው ጥበቃ እንደሚደረግለት አመላክተው ለዚህም ህገ-ወጥ ግንባታን በመከላከል ረገድ በቅንጅት እንደሚሰራም ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ጠቁመው ለዚህም የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ሲሉ ነው የተናገሩት።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026