የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በዞኑ ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል የአፈር ማዳበሪያ እየተሰራጨ ነው

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ለመጪው የመኸር ሰብል ልማት የሚውል ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ በማስገባት ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ለ2018/19 የመኸር ሰብል ልማት ተገቢውን ግብዓት በማቅረብ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።

በዚህም ለመጪው ምርት ዘመን ከ644 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ በተደረገ ጥረት እስካሁን ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ማስገባት መቻሉን ገልጸዋል።


ወደ ዞኑ ከገባው ውስጥም ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ ወደ ወረዳዎች በማድረስ ቅድሚያ ለሚዘሩትና ሩቅ አካባቢ ለሚገኙ አርሶ አደሮች እየተሰራጨ ነው ብለዋል።

ቀደም ብሎ ማዳበሪያው መሰራጨቱ አርሶ አደሩ ተረጋግቶ የዘር ሥራውን በወቅቱ ከማከናወን ባለፈ ምርታማነቱን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርም አስረድተዋል።

በአልብኮ ወረዳ የ014 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አብዱ እንድሪስ በሰጡት አስተያየት፣ ለቀጣይ የመኸር እርሻ ከሚያስፈልጋቸው እስካሁን 3 ኩንታል ማዳበሪያ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።


በዘንድሮው የመኸር ዘመን ሁለት ሄክታር ማሳቸውን በተለያየ ሰብል ለማልማት እየተዘጋጁ መሆኑን ጠቁመው ማዳበሪያው ቀድሞ በእጃችን መግባቱ ያለስጋት የእርሻ ስራችንን ለማከናወን ያግዘናል ብለዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን በ2018/19 የምርት ዘመን ከ432 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ16 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያሳያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026

<p>የባቡር መንገደኞች በፋይዳ መታወቂያ የትኬት አገልግሎት የሚያገኙበት ስርዓት ተግባራዊ ሊሆን ነው</p>

አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...

Feb 24, 2025