የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በዞኑ ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል የአፈር ማዳበሪያ እየተሰራጨ ነው

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ለመጪው የመኸር ሰብል ልማት የሚውል ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ በማስገባት ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ለ2018/19 የመኸር ሰብል ልማት ተገቢውን ግብዓት በማቅረብ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።

በዚህም ለመጪው ምርት ዘመን ከ644 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ በተደረገ ጥረት እስካሁን ከ300 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ማስገባት መቻሉን ገልጸዋል።


ወደ ዞኑ ከገባው ውስጥም ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ ወደ ወረዳዎች በማድረስ ቅድሚያ ለሚዘሩትና ሩቅ አካባቢ ለሚገኙ አርሶ አደሮች እየተሰራጨ ነው ብለዋል።

ቀደም ብሎ ማዳበሪያው መሰራጨቱ አርሶ አደሩ ተረጋግቶ የዘር ሥራውን በወቅቱ ከማከናወን ባለፈ ምርታማነቱን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርም አስረድተዋል።

በአልብኮ ወረዳ የ014 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አብዱ እንድሪስ በሰጡት አስተያየት፣ ለቀጣይ የመኸር እርሻ ከሚያስፈልጋቸው እስካሁን 3 ኩንታል ማዳበሪያ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።


በዘንድሮው የመኸር ዘመን ሁለት ሄክታር ማሳቸውን በተለያየ ሰብል ለማልማት እየተዘጋጁ መሆኑን ጠቁመው ማዳበሪያው ቀድሞ በእጃችን መግባቱ ያለስጋት የእርሻ ስራችንን ለማከናወን ያግዘናል ብለዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን በ2018/19 የምርት ዘመን ከ432 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ16 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያሳያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026