የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምዕራብ ጎንደር ዞን በማዕድን ዘርፍ ለወጣቶች የስራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ ተችሏል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦በምዕራብ ጎንደር ዞን በለውጡ መንግስት ልዩ ትኩረት በተሰጠው የማዕድን ዘርፍ ለወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ መቻሉ ተገለጸ።

​የዞኑ ማዕድን ሀብት መምሪያ ኃላፊ ተወካይና የማዕድን ሥራዎች ፈቃድ አስተዳደር ባለሙያ አቶ ወረቀት ቆየ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዞኑ እምቅ የማዕድንና ግብርና ኢንቨስትመንት ሃብት ያለው ነው።


በዚህም በዞኑ ባለፉት 9 ወራት ያለውን ማእድን ለማልማት በተደረገ ጥረት በ32 ማህበራት ለተደራጁ ከ470 በላይ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል።

የስራ ዕድሉን መፍጠር የተቻለውም በኦፓል፣ በጥቁር ድንጋይና በነጭ አሸዋ ማውጣት መሆኑን ተናግረዋል።

በዞኑ በተደጋጋሚ በተጠናው ጥናት መሰረት የወርቅ፣ የብረት፣ የኦፓል፣ የጄሶ፣ የሲልካ፣ የመዳብና የኒኬል ማዕድናት በስፋት እንደሚገኙ መረጋገጡን አስረድተዋል።


በቀጣይ ከክልሉ ጋር በመነጋገርና ባለሃብቶችን ወደ አካባቢው በመሳብ የማዕድን ሃብቱን በማልማት ተጨማሪ የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል።

ከማዕድን ልማቱም ገቢ በመሰብሰብ ለልማት ማዋል መቻሉን ጠቁመው የመጣውን ሰላም በመጠቀም በቀጣይ የስራ እድል ፈጠራውን ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።

​በገንዳውሃ አካባቢ በአሽዋና በድንጋይ ማዕድን ልማት ስራ ላይ በመደራጀት ወደ ስራ ከገቡ ወጣቶች መካከል ወጣት ዮሴፍ ዳኘ እንደገለጸው፤ በከተማዋ ለሚካሄደው የኮሪደር ልማት ግብዓት በማቅረብ ውጤታማ ሆነዋል።

በባህላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ዘርፍ ላይ የተሰማሩት አቶ ምህረት ደጀኔ በበኩላቸው፤ በመንግሥት በኩል እየተደረገላቸው ያለው ድጋፍ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይ ህገ-ወጥ የማዕድን ዝውውርን በመከላከልና የተደራጁ ዜጎች ሰርተው እንዲለወጡ እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026