የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምዕራብ ጎንደር ዞን በማዕድን ዘርፍ ለወጣቶች የስራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ ተችሏል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦በምዕራብ ጎንደር ዞን በለውጡ መንግስት ልዩ ትኩረት በተሰጠው የማዕድን ዘርፍ ለወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ መቻሉ ተገለጸ።

​የዞኑ ማዕድን ሀብት መምሪያ ኃላፊ ተወካይና የማዕድን ሥራዎች ፈቃድ አስተዳደር ባለሙያ አቶ ወረቀት ቆየ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዞኑ እምቅ የማዕድንና ግብርና ኢንቨስትመንት ሃብት ያለው ነው።


በዚህም በዞኑ ባለፉት 9 ወራት ያለውን ማእድን ለማልማት በተደረገ ጥረት በ32 ማህበራት ለተደራጁ ከ470 በላይ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል።

የስራ ዕድሉን መፍጠር የተቻለውም በኦፓል፣ በጥቁር ድንጋይና በነጭ አሸዋ ማውጣት መሆኑን ተናግረዋል።

በዞኑ በተደጋጋሚ በተጠናው ጥናት መሰረት የወርቅ፣ የብረት፣ የኦፓል፣ የጄሶ፣ የሲልካ፣ የመዳብና የኒኬል ማዕድናት በስፋት እንደሚገኙ መረጋገጡን አስረድተዋል።


በቀጣይ ከክልሉ ጋር በመነጋገርና ባለሃብቶችን ወደ አካባቢው በመሳብ የማዕድን ሃብቱን በማልማት ተጨማሪ የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል።

ከማዕድን ልማቱም ገቢ በመሰብሰብ ለልማት ማዋል መቻሉን ጠቁመው የመጣውን ሰላም በመጠቀም በቀጣይ የስራ እድል ፈጠራውን ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።

​በገንዳውሃ አካባቢ በአሽዋና በድንጋይ ማዕድን ልማት ስራ ላይ በመደራጀት ወደ ስራ ከገቡ ወጣቶች መካከል ወጣት ዮሴፍ ዳኘ እንደገለጸው፤ በከተማዋ ለሚካሄደው የኮሪደር ልማት ግብዓት በማቅረብ ውጤታማ ሆነዋል።

በባህላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ዘርፍ ላይ የተሰማሩት አቶ ምህረት ደጀኔ በበኩላቸው፤ በመንግሥት በኩል እየተደረገላቸው ያለው ድጋፍ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይ ህገ-ወጥ የማዕድን ዝውውርን በመከላከልና የተደራጁ ዜጎች ሰርተው እንዲለወጡ እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026