🔇Unmute
ደሴ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ቋሚ የሆኑ የፍራፍሬ ተክሎችን ለማልማት የችግኝ ተከላ ስራ መጀመራቸውንበኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የደዋጨፋ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።
የዞኑ አስተዳደር በበኩሉ ከሁለት ሺህ 300 ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም የፍራፍሬ ልማት ማረስ መጀመሩን አስታውቋል።
በዞኑ በደዋጨፋ ወረዳ የሸክላ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መሀመድ ሁሴን ለኢዜአ እንደገለጹት፣ አንድ ሄክታር ማሳቸውን በኩታ ገጠም በሙዝ ተክል በማልማት የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን እየሰሩ ነው።

እስካሁን ከ800 በላይ የተሻሻሉ የሙዝ ችግኞችን መትከላቸውን ጠቁመው፣ ችግኞቹ ጸድቀው ተገቢውን ምርት መስጠት እንዲችሉ እንክብካቤ እያደረጉ እንደሚገኙ አስረድተዋል።
በአካባቢው ዓመቱን ሙሉ የሚፈስ ወንዝ ቢኖርም እስካሁን እንዳልተጠቀሙበት ጠቁመው የተከሉት የሙዝ ችግኝ በዘጠኝ ወር ምርት የሚሰጥ በመሆኑ ተጠቃሚነታችንን የሚያረጋግጥ እንደሚሆንም እምነት አለኝ ብለዋል።
ሌላው የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት እንድሪስ ሁሴን በበኩሉ፤በሁለት ሔክታር መሬት ላይ መንግስት በነጻ ያቀረበላቸውን የተሻሻለ የፍራፍሬ ችግኝ በኩታ ገጠም እርሻ ማሳቸው እያለሙ እንደሚገኙ ተናግሯል።

ከፍራፍሬ ተክሎቹ ውስጥ ሙዝና ፓፓያን እያለማ ሲሆን እስካሁን አንድ ሺህ 600 የሙዝ ችግኞችን ለመትከል ችያለሁ ነው ያለው።
በአካባቢው ቀድመው በፍራፍሬ ልማት ስራ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች በተሻለ መንገድ ተጠቃሚ መሆናቸውን በማየት ወደ ሙዝ ልማቱ መግባታቸውን ገልጿል።
ግማሽ ሄክታር ማሳዬን በፍራፍሬ ለማልማት የሙዝ ችግኞችን መትከል ጀምሪያለሁ ያሉት ደግሞ በወረዳው የገርቢ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አህመድ ኡመር ናቸው።

መንግስት በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጥ፣ ምርታማና በሽታን የሚከላከል የሙዝ ዝርያ በነጻ ያቀረበልን በመሆኑ ተገቢውን እንክብካቤ አድርገን የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን እየሰራን ነው ብለዋል።
የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው፣ በዞኑ ፍራፍሬ በስፋት በማልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅትም ከሁለት ሺህ 300 ሄክታር በላይ መሬት በኩታገጠም እርሻ ፍራፍሬን የማልማት ሥራ መጀመሩንም ነው ያስረዱት።
ልማቱን ለማሳለጥም ለአርሶ አደሩ በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጥ፣ በሽታን የሚከላከልና ምርታማ የሆኑ የሙዝ ችግኝ በነጻ ማቅረብ መቻሉን አመላክተዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026