የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የደዋጨፋ ወረዳ አርሶ አደሮች ቋሚ የሆኑ የፍራፍሬ ተክሎችን ለማልማት የችግኝ ተከላ ስራ ጀምረዋል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ቋሚ የሆኑ የፍራፍሬ ተክሎችን ለማልማት የችግኝ ተከላ ስራ መጀመራቸውንበኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የደዋጨፋ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።

የዞኑ አስተዳደር በበኩሉ ከሁለት ሺህ 300 ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም የፍራፍሬ ልማት ማረስ መጀመሩን አስታውቋል።

በዞኑ በደዋጨፋ ወረዳ የሸክላ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መሀመድ ሁሴን ለኢዜአ እንደገለጹት፣ አንድ ሄክታር ማሳቸውን በኩታ ገጠም በሙዝ ተክል በማልማት የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን እየሰሩ ነው።


እስካሁን ከ800 በላይ የተሻሻሉ የሙዝ ችግኞችን መትከላቸውን ጠቁመው፣ ችግኞቹ ጸድቀው ተገቢውን ምርት መስጠት እንዲችሉ እንክብካቤ እያደረጉ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

በአካባቢው ዓመቱን ሙሉ የሚፈስ ወንዝ ቢኖርም እስካሁን እንዳልተጠቀሙበት ጠቁመው የተከሉት የሙዝ ችግኝ በዘጠኝ ወር ምርት የሚሰጥ በመሆኑ ተጠቃሚነታችንን የሚያረጋግጥ እንደሚሆንም እምነት አለኝ ብለዋል።

ሌላው የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት እንድሪስ ሁሴን በበኩሉ፤በሁለት ሔክታር መሬት ላይ መንግስት በነጻ ያቀረበላቸውን የተሻሻለ የፍራፍሬ ችግኝ በኩታ ገጠም እርሻ ማሳቸው እያለሙ እንደሚገኙ ተናግሯል።


ከፍራፍሬ ተክሎቹ ውስጥ ሙዝና ፓፓያን እያለማ ሲሆን እስካሁን አንድ ሺህ 600 የሙዝ ችግኞችን ለመትከል ችያለሁ ነው ያለው።

በአካባቢው ቀድመው በፍራፍሬ ልማት ስራ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች በተሻለ መንገድ ተጠቃሚ መሆናቸውን በማየት ወደ ሙዝ ልማቱ መግባታቸውን ገልጿል።

ግማሽ ሄክታር ማሳዬን በፍራፍሬ ለማልማት የሙዝ ችግኞችን መትከል ጀምሪያለሁ ያሉት ደግሞ በወረዳው የገርቢ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አህመድ ኡመር ናቸው።


መንግስት በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጥ፣ ምርታማና በሽታን የሚከላከል የሙዝ ዝርያ በነጻ ያቀረበልን በመሆኑ ተገቢውን እንክብካቤ አድርገን የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን እየሰራን ነው ብለዋል።

የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው፣ በዞኑ ፍራፍሬ በስፋት በማልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በአሁኑ ወቅትም ከሁለት ሺህ 300 ሄክታር በላይ መሬት በኩታገጠም እርሻ ፍራፍሬን የማልማት ሥራ መጀመሩንም ነው ያስረዱት።

ልማቱን ለማሳለጥም ለአርሶ አደሩ በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጥ፣ በሽታን የሚከላከልና ምርታማ የሆኑ የሙዝ ችግኝ በነጻ ማቅረብ መቻሉን አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026