🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በሳይንስና ፈጠራ የበለፀገ ትውልድ መገንባት ለሀገር ብልጽግና እና ሁለንተናዊ እድገት መሰረት በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ “በሳይንስና ፈጠራ የተካነ ትውልድ ለተምሳሌታዊ ሀገር” በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 11ኛው የሳይንስና የፈጠራ ሥራ ዐውደ-ርዕይ በአራዳ ፓርክ እየተካሄደ ይገኛል።
በዚህ መድረክ ላይ በርካታ ተማሪዎችና መምህራን የፈጠራ ሥራዎቻቸውን ለዕይታ አቅርበዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዐውደ-ርዕዩን በጎበኙበት ወቅት እንደተናገሩት፤ መድረኩ ተማሪዎችና መምህራን የፈጠራ ሥራዎቻቸውን የሚያስተዋውቁበትና እርስበርስ የፈጠራ ሐሳባቸውን የሚለዋወጡበት ወሳኝ ድልድይ ነው።
በዐውደ-ርዕዩ የቀረቡት የፈጠራ ውጤቶች ከተማዋን ወደ ስማርት ሲቲ ለመቀየር እየተደረገ ላለው ጥረት ትልቅ ተስፋ የሚሰጥና የምሥራች መሆናቸውንም ገልጸዋል።
ማንኛውም የፈጠራ ሥራ ውጤት በትንሽ ጅማሮ የሚነሳ መሆኑን ጠቅሰው፤ መንግሥት እነዚህን የፈጠራ ሥራዎች በፋይናንስና በሙያ በመደገፍ ወደ ላቀ ደረጃ እንዲሸጋገሩ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
በአሁኑ ወቅት በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች በሳይንስና በቴክኖሎጂ የታገዙ እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑንም አክለዋል።
ዐውደ-ርዕዩ የፈጠራ ውጤቶችን ወደ ተግባር በመቀየር የሀገርን ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጉዞ እንደሚያፋጥን ታምኖበታል ነው ያሉት።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) እንደገለጹት መድረኩ ተማሪዎች ዕውቀት የሚያገኙበት ብቻ ሳይሆን፤ የጥበብ ባለቤት መሆናቸውን በተግባር የሚያሳዩበት ነው።
ባለፉት ዓመታት ጥቂት ተማሪዎች ይሳተፉበት የነበረው የምርምርና ፈጠራ ሥራ ዛሬ የብዙዎች ባህልና ጉጉት መሆኑን መድረኩ ማረጋገጡንም ጠቁመዋል።
ይህ የፈጠራ እድገት በከተማዋ በስፋት ከሚከናወኑ መሠረተ-ሰፊ የልማት ሥራዎችና ፕሮጀክቶች ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑንም አብራርተዋል።

የቅድመ-1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በዓይነትና በጥራት መስፋፋታቸው ሕፃናት በራስ የመተማመን ስሜት ትምህርታቸውን እንዲጀምሩና ለሳይንስ ሥራዎች ጠንካራ መሠረት እንዲጥሉ እያደረገ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026