የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

አዲስ አበባን የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Apr 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- አዲስ አበባን የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል የሚያደርጉ ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ከንቲባ አዳነች ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ 11ኛውን ከተማ አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ በይፋ ከፍተዋል።


“በሳይንስና ፈጠራ የተካነ ትውልድ ለተምሳሌታዊ ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የሚደረገው አውደ ርዕይ ዛሬ እና ነገ ክፍት ሆኖ ይቆያል።

ከንቲባዋ አውደ ርዕዩን በከፈቱበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ መድረኩ የከተማዋን የፈጠራ ጉዞ አንድ ደረጃ የሚያራምድ መሆኑን ገልጸዋል።

የዛሬው የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ዋነኛ ዓላማ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን ትምህርት በተግባር የሚያሳዩበት መድረክ መፍጠር እንደሆነ አመልክተዋል።

አያይዘውም ተማሪዎች የውስጥ ተሰጥዖዋቸውን የሚገልጹበት፣ ለሰሯቸው የፈጠራ ስራዎች ዕውቅናና ማበረታቻ የሚያገኙበት እንዲሁም እርስ በእርስ በትብብር የመስራት ልምድ የሚለዋወጡበት ትልቅ መድረክ ነው ብለዋል።


እውነተኛ እውቀት ችግሮችን ደጋግሞ ማውራት ሳይሆን ለችግሮች መፍትሄ ማፍለቅና ችግርን ወደ ድል መቀየር መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባ አዳነች፣ አዲስ አበባን የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል ለማድረግ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

አሁን ላይ የተጀመሩ ስራዎች ውጤት በተጨባጭ መታየት የጀመረበት ወቅት ላይ መደረሱን ገልጸው፣ ይህ ውጤታማ ጅምር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ዛሬ የፈጠራ ስራቸውን ያቀረቡ ተማሪዎችና መምህራን ላይ ትልቅ ተስፋ እንዳላቸው የገለጹት ከንቲባዋ፣ እነዚህ የፈጠራ ስራዎች አድገውና በልጽገው ለከተማዋ፣ለሀገር ብሎም ለዓለም የሚተርፍ በረከት እንደሚሆኑ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026