የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

አዲስ አበባን የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Apr 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- አዲስ አበባን የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል የሚያደርጉ ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ከንቲባ አዳነች ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ 11ኛውን ከተማ አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ በይፋ ከፍተዋል።


“በሳይንስና ፈጠራ የተካነ ትውልድ ለተምሳሌታዊ ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የሚደረገው አውደ ርዕይ ዛሬ እና ነገ ክፍት ሆኖ ይቆያል።

ከንቲባዋ አውደ ርዕዩን በከፈቱበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ መድረኩ የከተማዋን የፈጠራ ጉዞ አንድ ደረጃ የሚያራምድ መሆኑን ገልጸዋል።

የዛሬው የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ዋነኛ ዓላማ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን ትምህርት በተግባር የሚያሳዩበት መድረክ መፍጠር እንደሆነ አመልክተዋል።

አያይዘውም ተማሪዎች የውስጥ ተሰጥዖዋቸውን የሚገልጹበት፣ ለሰሯቸው የፈጠራ ስራዎች ዕውቅናና ማበረታቻ የሚያገኙበት እንዲሁም እርስ በእርስ በትብብር የመስራት ልምድ የሚለዋወጡበት ትልቅ መድረክ ነው ብለዋል።


እውነተኛ እውቀት ችግሮችን ደጋግሞ ማውራት ሳይሆን ለችግሮች መፍትሄ ማፍለቅና ችግርን ወደ ድል መቀየር መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባ አዳነች፣ አዲስ አበባን የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል ለማድረግ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

አሁን ላይ የተጀመሩ ስራዎች ውጤት በተጨባጭ መታየት የጀመረበት ወቅት ላይ መደረሱን ገልጸው፣ ይህ ውጤታማ ጅምር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ዛሬ የፈጠራ ስራቸውን ያቀረቡ ተማሪዎችና መምህራን ላይ ትልቅ ተስፋ እንዳላቸው የገለጹት ከንቲባዋ፣ እነዚህ የፈጠራ ስራዎች አድገውና በልጽገው ለከተማዋ፣ለሀገር ብሎም ለዓለም የሚተርፍ በረከት እንደሚሆኑ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026