የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያ የአቪዬሽን መሰረተ ልማት በማሟላት የአፍሪካ አቪዬሽን መግቢያ በር መሆን የሚያስችላት ቁመና ላይ ናት

Apr 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የአቪዬሽን መሰረተ ልማት በማሟላት የአፍሪካ አቪዬሽን መግቢያ በር መሆን የሚያስችላት ቁመና ላይ ናት ሲሉ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሀሰን ገለጹ።

ዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባኤ በአፍሪካ አቪዬሽን ዘርፍ ባሉ ችግሮች እና መፍትሔዎች ላይ ምክክር ይደረጋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሀሰን እንደገለጹት፤ አፍሪካ አንድ ነጥብ አራት ቢሊየን የህዝብ ቁጥር ያላት ቢሆንም አህጉሪቱ በበቂ መጠን በአየር ትራንስፖርት ተሳስራለች ማለት አይቻልም።


ለዚህም የዋጋ መጨመር፣ የመሰረተ ልማት በበቂ ደረጃ አለመሟላት እና ወጥ የሆነ የአሰራር ስርዓት አለመኖር ዋነኞቹ ምክንያቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ እንደ ሀገር በአቪዬሽን መሰረተ ልማት ላይ በሰፊው ኢንቨስት በማድረግ ላይ መሆኗን በመጠቆም፤ በቢሾፍቱ ግንባታው የተጀመረው ዓለምአቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክትም ተጠቃሽ መሆኑን ገልጸዋል።

ግንባታው ሲጠናቀቅም የኢትዮጵያን አቅም ከማሳደጉ ባሻገር አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር ለማስተሳሰር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ዘርፍ መሰረተ ልማት ላይ የምታከናውነው ሥራ ሀገሪቷን የአፍሪካ አቪዬሽን መግቢያ በር (ጌት ዌይ) የሚያደርጋት መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በጠንካራ ሪፎርም ውስጥ እንዲያልፍ መደረጉን ጠቁመው፤ ይህም በኢትዮጵያ ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ የበረራ አገልግሎት እንዲኖር በማድረግ ጠንካራ ተቆጣጣሪ ተቋም እንዲፈጠር ማስቻሉን አብራርተዋል።

በአፍሪካ አቪዬሽን ዘርፍ ለሚስተዋሉ ችግሮች ዘላቂ እልባት ለማበጀት በጋራ መስራት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ችግሮችን ከመለየት ባለፈ ተግባራዊ የመፍትሔ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ኢትዮጵያም በመስኩ ያሉ ማነቆዎች እንዲፈቱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗንም አረጋግጠዋል።


የዓለም አቀፍ ሲቪል አቪየሽን ድርጅት የምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ሉሲ ቡግዋ በበኩላቸው፤ የአፍሪካን የአቪየሽን ትስስር ለማፋጠን ሀገራት በትብብር ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።

በአፍሪካ ደኅንነቱ የተጠበቀ የአቪየሽን መሠረተ ልማት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።


የአፍሪካ አየር መንገዶች ማኅበር ዋና ጸኃፊ አብድራህማን በርቴ፤ የአህጉሪቱን የበራራ ግንኙነት ለማፋጠን በርካታ ሀገራት የአፍሪካ የተቀናጀ የአየር ትራንስፖርት ገበያ የትብብር ማዕቀፍ መፈረማቸውን ገልጸዋል።

ሀገራቱም የትብብር ስምምነት ማዕቀፉን ከመፈረም ባሻገር ወደ ተግባር እንዲለወጥ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ አህጉሪቱን በአቪየሽን ልማት በማስተሳሰር የሚጠበቅበትን ገንቢ ሚና እየተወጣ ነው ብለዋል።

በቀጣይም ከአፍሪካ የአቪየሽን ኢንዱስትሪ ተዋናዮች ጋር በመተባበር አህጉሪቱን ለማስተሳሰር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026