የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ የፈጠራ ሥራዎችን በመደገፍ ለሁለንተናዊ ልማት ያላቸውን አበርክቶ ለማሳደግ የተጀመረው ጥረት ይጠናከራል

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቡታጅራ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ሥራዎችን በመደገፍ ለሁለንተናዊ ልማት ያላቸውን አበርክቶ ለማሳደግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ።

በክልሉ "ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን የሳይንስ፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የውይይት መድረክና አውደ ርዕይ በቡታጅራ ከተማ ተካሂዷል።


በመድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ አንተነህ ፈቃዱ እንደገለጹት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤቶች ለሁለንተናዊ የልማት ስራዎች ፋይዳቸው የጎላ ነው።

በክልሉም ግብርናና ኢንዱስትሪን ጨምሮ በሌሎች የልማት መስኮች የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በመፍታት በኩል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በመሆኑም በክልሉ የፈጠራ ሥራዎችን በመደገፍ ለሁለንተናዊ ልማት የሚኖራቸውንአበርክቶ ለማሳደግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


በዘርፉ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በትምህርት ተቋማት ላይ ይበልጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልጸዋል።


የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ሀላፊ ሰላሙ አማዶ በበኩላቸው እንዳሉት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች የማህበረሰቡን ችግር በመፍታት በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረጉ ነው።

የፈጠራ ባለቤቶችን በማበረታታትና ተጠቃሚነታቸውን በማሳደግ በዘርፉ እየተመዘገበ ያለውን ስኬት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።


የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የምርምር ሥራዎችን ለኢንዱስትሪዎች በማሸጋገር ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ ማድረግ ይገባልያሉት ደግሞ የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ ሙስጠፋ ኢሳ ናቸው።

በክልሉ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎችን ከማፍለቅ በተጨማሪ ተኪ ምርት በማምረት በኩል የሚጠበቅባቸውን ሚና እየተወጡ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ኢንተርፕራይዞቹ ለሌሎች ወጣቶችም የሥራ ዕድል እየፈጠሩ መሆኑን ጠቁመው፣ የዘርፉን ስኬቶች ለማጠናከር ቢሮው አበክሮ ይሰራል ብለዋል።

ከዚህ ቀደም በምርምር ለከናወነው የተፈጥሮ ማዳበሪያ በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና እንደተሰጠው የተናገረው ወጣት ተመስገን በቀለ፣ በክልሉ በተደረገለት ድጋፍና ክትትል በእንሰት በሽታ መከላከል የሚያስችል ምርምር ማድረጉን ተናግሯል።

በመድረኩ ማጠቃለያ በቡታጅራ ከተማ በተዘጋጀ 3ኛው ዙር ክልላዊ የሳይንስና የፈጠራ ሥራዎች አውደ ርዕይ ለእይታ ከቀረቡ 146 የፈጠራ ሥራዎች ለተሻሉት እውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026