የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ

Jun 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት ለህብረተሰቡ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

የሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ የማዕከሉን ተደራሽነት በማስፋት መንግስታዊ አገልግሎቶችን በጥራትና በፍጥነት ለመስጠት የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በማቅረብ የማህበረሰቡን እንግልት በማስቀረት በኩል ያለው አስተዋጽኦ ጉልህ መሆኑንም ተናግረዋል።

ማዕከሉ ዜጎች መንግስታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደተለያዩ ቢሮዎች የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ከማስቀረት በተጨማሪ ለከተሞች ፈጣን እድገት መረጋገጥ በጎ ተፅዕኖ እንዳለውም አመልክተዋል።


በመሆኑም በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ ከተሞች ማዕከላቱ ተገንብተው ለአገልግሎት እንዲበቁ በክልሉ መንግስት በኩል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የክልሉ መንግስት ከማህበረሰቡ ለተነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት የጀመረውን ተግባር አጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።

የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ በበኩላቸው እንዳሉት፤ በዞኑ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።


መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራርን በማስቀረት ለማህበረሰቡ ፈጣን፣ ዘመናዊና ከሙስና የጸዳ አገልግሎት ለመስጠት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።

ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው የሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ጉልህ ጠቀሜታ እንዳለውም ገልጸዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሳሙኤል ሽጉጤም መንግስት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።


በከተማ አስተዳደሩ ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት ዛሬ የተመረቀው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ በማቅረብ የማህበረሰቡን እንግልት እንደሚያስቀር ገልጸዋል።

በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የክልል፣ የሀድያ ዞን እና የሆሳዕና ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026