🔇Unmute
ቴፒ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር ያወጣቸውንና ለቆላማ አካባቢዎች ተስማሚ የሆኑ የቡና ዝርያዎችን እያስፋፋ መሆኑን አስታወቀ።
የምርምር ማዕከሉ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ አላሞ ቀበሌ ላይ በአርሶ አደሮች ማሳ ያላመዳቸውን የቡና ተክሎች ምልከታና የልምድ ልውውጥ አድርጓል።
በማዕከሉ የሰብል ምርምር ሥራ ሂደት አስተባባሪ ሸሐሚል አሎ እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ከቡና ልማት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በምርምር ያወጣቸውን የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ የማላመድ ሥራ እየሰራ ነው።

በምርምር የተገኙት ውጤታማ የቡና ዝርያዎችም በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡና ለቆላማ አየር ንብረት ተስማሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የቡና ዝርያዎቹ በምርታማነታቸው የተረጋገጡ ከመሆናቸውም በላይ አርሶ አደሮች በጥራት በማምረት በገበያ ተወዳዳሪ የሚሆኑበትን እቅም እንደሚያጠናክሩም ጠቁመዋል።
እነዚህ በምርምር የተገኙ "K-1"፣ "K-2" እና " I-2" የተሰኙ የቡና ዝርያዎች ምርታማነታቸው ከነባሩ ዝርያ በእጥፍ ከፍ ያሉ መሆኑን አስተባባሪው ገልጸዋል።
የቡናው ዝርያ ውጤታማነት በማሳ ላይ በመረጋገጡ ወደ ሌሎች የአርሶ አደሮች ማሳ ለማስፋፋት ታቅዶ እንቅስቃሴ መጀመሩንም ተናግረዋል።
በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ባለሙያ አቶ ፍስሐ ግዛው፤ በወረዳው የቡና አመራረትን በማዘመን የውጭ ምንዛሬ አቅምን ከፍ ለማድረግ ከምርምር ማዕከሉ ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

በወረዳው የአላሞ ቀበሌ አርሶ አደር ይንገሥ ጌታቸው ከምርምር ማዕከሉ የወሰዱትን የቡና ዝርያዎች በአምስት ሔክታር መሬታቸው ላይ እያለሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የቡና ዝርያው በፍጥነት አድጎ ምርት ከመስጠቱ ባለፈ ለእንክብካቤና ለለቀማ ምቹ በመሆኑ ሥራውን ለማስፋፋት ከሚያደርጉት ጥረት ባለፈ ልምዳቸውን ለሌሎች አርሶ አደሮች እያጋሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ከማዕከሉ የተረከቡት የተሻሻለ የቡና ዝርያ ምርታማ በመሆኑ ነባሮቹን የቡና ማሳዎች በአዲስ እየተኩ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ አርሶ አደር ብርሃኑ ጌታቸው ናቸው።

በተሻሻለ የቡና ማሳ ልማት ላይ ልምድ የወሰዱ አርሶ አደሮች በበኩላቸው እንዳሉት፤ በመስክ ምልክታው በቀጣይ የቡና ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የሚያስችል ተሞክሮ አግኝተዋል።
ይህን ልምድ በመውሰድ ከዘንድሮ ክረምት ጀምሮ የተሻሻሉ የቡና ዝርያ ችግኞችን ከምርምር ማዕከሉ በመውሰድ ለመትከል መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026