🔇Unmute
ቴፒ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር ያወጣቸውንና ለቆላማ አካባቢዎች ተስማሚ የሆኑ የቡና ዝርያዎችን እያስፋፋ መሆኑን አስታወቀ።
የምርምር ማዕከሉ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ አላሞ ቀበሌ ላይ በአርሶ አደሮች ማሳ ያላመዳቸውን የቡና ተክሎች ምልከታና የልምድ ልውውጥ አድርጓል።
በማዕከሉ የሰብል ምርምር ሥራ ሂደት አስተባባሪ ሸሐሚል አሎ እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ከቡና ልማት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በምርምር ያወጣቸውን የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ የማላመድ ሥራ እየሰራ ነው።

በምርምር የተገኙት ውጤታማ የቡና ዝርያዎችም በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡና ለቆላማ አየር ንብረት ተስማሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የቡና ዝርያዎቹ በምርታማነታቸው የተረጋገጡ ከመሆናቸውም በላይ አርሶ አደሮች በጥራት በማምረት በገበያ ተወዳዳሪ የሚሆኑበትን እቅም እንደሚያጠናክሩም ጠቁመዋል።
እነዚህ በምርምር የተገኙ "K-1"፣ "K-2" እና " I-2" የተሰኙ የቡና ዝርያዎች ምርታማነታቸው ከነባሩ ዝርያ በእጥፍ ከፍ ያሉ መሆኑን አስተባባሪው ገልጸዋል።
የቡናው ዝርያ ውጤታማነት በማሳ ላይ በመረጋገጡ ወደ ሌሎች የአርሶ አደሮች ማሳ ለማስፋፋት ታቅዶ እንቅስቃሴ መጀመሩንም ተናግረዋል።
በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ባለሙያ አቶ ፍስሐ ግዛው፤ በወረዳው የቡና አመራረትን በማዘመን የውጭ ምንዛሬ አቅምን ከፍ ለማድረግ ከምርምር ማዕከሉ ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

በወረዳው የአላሞ ቀበሌ አርሶ አደር ይንገሥ ጌታቸው ከምርምር ማዕከሉ የወሰዱትን የቡና ዝርያዎች በአምስት ሔክታር መሬታቸው ላይ እያለሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የቡና ዝርያው በፍጥነት አድጎ ምርት ከመስጠቱ ባለፈ ለእንክብካቤና ለለቀማ ምቹ በመሆኑ ሥራውን ለማስፋፋት ከሚያደርጉት ጥረት ባለፈ ልምዳቸውን ለሌሎች አርሶ አደሮች እያጋሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ከማዕከሉ የተረከቡት የተሻሻለ የቡና ዝርያ ምርታማ በመሆኑ ነባሮቹን የቡና ማሳዎች በአዲስ እየተኩ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ አርሶ አደር ብርሃኑ ጌታቸው ናቸው።

በተሻሻለ የቡና ማሳ ልማት ላይ ልምድ የወሰዱ አርሶ አደሮች በበኩላቸው እንዳሉት፤ በመስክ ምልክታው በቀጣይ የቡና ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የሚያስችል ተሞክሮ አግኝተዋል።
ይህን ልምድ በመውሰድ ከዘንድሮ ክረምት ጀምሮ የተሻሻሉ የቡና ዝርያ ችግኞችን ከምርምር ማዕከሉ በመውሰድ ለመትከል መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026