🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018(ኢዜአ) ፦ በሀረር ከተማ የተጀመረው ሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭ በመደመር መንግስት እይታ ጥራትና ፍጥነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በሀረር ከተማ እየተገነባ የሚገኘውን የሀኪም ጋራ ኢኒሼቲቭን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በመስክ ምልከታው ላይም ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለፁት በአው ሀኪም ተራራ ላይ እየተሰራ የሚገኘው ኢኒሼቲቩ የአዲሲቷ ሀረር አለም አቀፍ ምልክት ከመሆን ባሻገር ለክልሉ የቱሪዝም ዘርፍ እድገት ጉልህ ፋይዳ ያበረክታል።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅም ለቱሪዝም መዳረሻነትና ለህዝብ መዝናኛነት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም የፕሮጀክቱ እውን መሆን የጎብኚዎችን ቆይታ በመጨመር ተጠቃሚነትን ከማሳደግ አንፃርም ሚናው ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።
በፕሮጀክቱም 1ሺህ 870 ደረጃዎች እንደሚኖሩት እና ሁለት ኪሎ ሜትር የሚጠጋ የመሰረተ ልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ አካባቢያዊ ሀብቶችን በመጠቀም እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
ተራራው ራሱን የቻለ የህግ ማዕቀፍ እንዲኖረው በማድረግ ተገቢው ጥበቃ እንደሚደረግለት አመላክተው ለዚህም ህገ-ወጥ ግንባታ በመከላከል ረገድ በቅንጅት እንደሚሰራም ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ተራራውን አረንጓዴ የማልበስ ስራ ይሰራል ብለዋል።
ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመው ለዚህም የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ሲሉ ነው የተናገሩት።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026