የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ባለፉት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች ትምህርት ቤቶች የውስጥ ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ ዕድል ፈጥረዋል

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ባለፉት ዓመታት የተከሏቸው ችግኞች የአካባቢን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የውስጥ ገቢያቸውን ለማሳደግ ዕድል መፍጠሩን በዲላ ከተማ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ገለጹ።

በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ዘርፍ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች የተራቆቱ አካባቢዎችን ገጽታ በአረንጓዴ ከመሸፈን ባለፈ ለውበትና ለገቢ ምንጭ እየሆኑ ነው።

በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከደን፣ ከጥላና ከውበት ዛፎች በተጨማሪ የገቢ ምንጭ ለሚሆኑ ተክሎች ትኩረት መሰጠቱ ከመርሀግብሩ የሚገኘውን ጥቅም ዘርፈ ብዙ እያደረገው ነው።


መርሀግብሩ የተፋሰስ ልማት ከተከናወነባቸው ስፍራዎች በተጨማሪ በከተሞች ክፍት ይዞታዎችና በተቋማትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።

በዲላ ከተማ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር በተከሏቸው ችግኞች ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጸዋል።

ትምህርት ቤቶቹ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የተከሏቸው ችግኞች የትምህርት ቤቱን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የውስጥ ገቢያቸውን እያሳደገው መምጣቱን ነው የተናገሩት።


የዲላ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ደሳለኝ ታፈሰ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በትምህርት ቤቱ ያሉትን ባዶ ቦታዎች በአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ችግኞችን በመትከል የተሞክሮ ማዕከል ማድረግ ተችሏል።

በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ በመርሀግብሩ የተተከሉ የቡና፣ የእንሰትና የፍራፍሬ ችግኞች የትምህርት ቤቱን ገጽታ እንደቀየሩና የውስጥ ገቢን እያሳደጉ መምጣታቸውን አንስተዋል።


በአሁኑ ወቅት ከቡናና ከፍራፍሬ ምርት ሽያጭ በዓመት ከ120 ሺህ ብር በላይ ገቢ ትምህርት ቤቱ እንደሚያገኝ ገልጸው፣ ልማቱ ተግባር ተኮር ትምህርት ለመስጠት ጭምር እየዋለ ነው ብለዋል።

አረንጓዴ አሻራ መርሀግብር የትምህርት ቤታቸውን ባዶ ቦታ እንዲለማና ገቢ ማስገኛም ሆኗል ያሉት ደግሞ በዲላ ከተማ የዳዊት 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕስ መምህርት መሠረት ተሰማ ናቸው።


ለጥላ ዛፍ የሚሆኑ ዛፎች ከመተከላቸው በተጨማሪ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ለምርት መድረሳቸውን ጠቅሰው ይህም የውስጥ ገቢን በማሳደግ ድርሻው የጎላ ነው ብለዋል።

የዲላ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ ኡውዩ ሃይሉ በበኩላቸው እንዳሉት፤ በከተማው ከ30 ሄክታር በላይ የትምህርት ቤቶች ይዞታ በአረንጓዴ አሻራ እንዲለማ ተድርጓል።


በተለይ ለምግብነት የሚሆኑ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ቡናና እንሰት የትምህርት ቤቶችን ገጽታ ከመቀየር በተጨማሪ የገቢ ምንጭ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

በተያዘው ዓመትም ይህንን ተሞክሮ በማስፋት ዘርፈ ብዙ ጠቄሜታ ያላቸውን ችግኞች በሌሎች ትምህርት ቤቶችም ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026