የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የቡና ልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እያስቻለ ነው

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ወለጋ እና ጅማ ዞኖች የቡና ልማትን ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጋር ለማስተሳሰር የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ማስገኘታቸውን የየዞኖቹ ግብርና ጽህፈት ቤቶች አስታወቁ።

የጅማ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሚፍታህ ገሊ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዞኑ ባሉ 21 ወረዳዎች የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ ይገኛል።


የቡና ልማቱን ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጋር ለማስተሳሰር እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል።

ከዚህ ውስጥም በቡና ልማት ስራ ላይ የተሳተፉ ከ400 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ምርታማነታቸውን በሄክታር በአማካይ ከ11 እስከ 13 ኩንታል ለማሳደግ መቻላቸውን አብራርተዋል።

በዞኑ እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት 300 ሺህ ቶን ቡና ተመርቶ ለማእከላዊ ገበያ እና ለሀገር ውሰጥ ፍጆታ እየቀረበ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

በተያዘው ዓመት የቡና ልማቱን ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጋር በማስተሳሰር ይበልጥ ለማስፋፋት እንዲቻል ከ700 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።

በአሁኑ ወቅትም በዞኑ 513 ቀበሌዎች በመተከል ላይ ባሉት የቡና ችግኞችም 90 ሺህ ሄክታር አዲስ መሬት የሚለማ እና ይህም በዘርፉ የነበረውን ሽፋን እንደሚያሳድግም ገልጸዋል።

የምእራብ ወለጋ ዞን የግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ቡላ ደመራ፤ በዞኑ ቡናን በክላስተር የማልማት ኢንሼቲቭ ተግባራዊ መደረጉ አርሶ አደሩ ከዘርፉ የተሻለ ምርት እንዲያገኝ እያደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።


በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም 32 ሚሊዮን የተሻሻሉ የቡና ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን በሄክታር ከ 2 ሺህ 500 እስከ 5 ሺህ ችግኝ እንደሚተከልም ነው የተናገሩት።

በዚሁ ወቅት 64 ሺህ 551 ሄክታር አዲስ መሬት እንደሚለማ ገልጸው አርሶ አደሩ ያረጁ ቡናዎችንም በመጎንደል በአዲስ እንዲተካ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መሀመድ ሳኒ በበኩላቸው፤ በክልሉ የሚካሔዱ የቡና ልማት ስራዎችን ለማስፋፋት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል።


ይህንን ለማጠናከርም በዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከ 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ የቡና ችግኝ ይተከላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026