🔇Unmute
ሀዋሳ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማት ፀጋዎቿን አጉልቶ ያሳየ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለፁ፡፡
በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተጀመረው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የመልማት አቅማቸውን ወደ ተግባር በመለወጥ ለትውልድ የሚሻገር ሰው ተኮር የልማት ውጤቶች እንዲመዘገቡ እያደረገ ነው።
የዚሁ አካል የሆነው የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማትም ተፈጥሯዊ ሀብቶቿን በማልማት ፈጣን ዕድገት እንድታስመዘግብ አድርጓል።

የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የከተማዋ የኮሪደር ልማት በተፈጥሮ ከታደለቻቸው ሐይቅና ተራሮች ጋር የተሳሰረና በፕላን ላይ የተመሰረተ ሰው ተኮር ልማት እንዲተገበር አግዟል።
ልማቱ ሰፋፊ መንገዶችና አረንጓዴ ሥፍራዎች እንዲስፋፉ በማድረግ በከተማዋ የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምርና ለሥራና ለኑሮ ተመራጭ ከተማ እንድትሆን ማድረጉን ተናግረዋል፡፡
በኮሪደር ልማቱ የተገነቡ የእግረኛና ብስክሌት መንገዶች ሀዋሳ ቀድሞ የነበራትን የብስክሌት ባህል ዳግም እንዲያንሰራራ ያደረገ መሆኑን ከንቲባው ጠቁመዋል፡፡
የሕፃናት መጫወቻዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ የብስክሌት መንገዶች፣ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ የታክሲ መጫኛና ማውረጃዎች እንዲሁም ሌሎች ከተማዋን ዘመናዊነት የሚያላብሱ ሥራዎች በኮሪደር ልማቱ መካተታቸውንም ገልጸዋል፡፡
ልማቱን ከቱሪስት መዳረሻ ተፈጥሯዊ መስህቦቿ ጋር እንዲተሳሰር ለማድረግም የሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡

የሀዋሳ ከተማ ለመዝናኛ ተመራጭ የሚያደርጋት ተፈጥሯዊና ሰውሰራሽ መስህቦች ባለቤት እንደሆነች የተናገሩት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ወጋየሁ ሰለሞን ናቸው።
አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ የሕፃናት መዝናኛ ሥፍራዎችም ይህን አቅሟን የሚያሳድጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

ቀደም ሲል የቆሸሹ አካባባዎችና ለወንጀል መፈጸሚያ ምቹ የነበሩ ቦታዎች ጭምር ወደ ልማት መግባታቸው የከተማዋን እድገት ለመፋጠን ካላቸው ፋይዳ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን እያሳደጉ ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ ቀደም ሲል በከተማዋ የነበረውን ጠባብ የእግረኛ መንገድ ማስቀረቱ የሚበረታታ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ይሄይስ ወንድሙ የተባሉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ናቸው።

ይህም በእግር በመንቀሳቀስ ጤናን ለመጠበቅና የከተማዋን የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ ማገዙን ጠቁመዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የዜጎችን ጤና ለመጠበቅና በከተማዋ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች እንዲነቃቁ ማገዙን አስረድተዋል፡፡
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026