🔇Unmute
ሀዋሳ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማት ፀጋዎቿን አጉልቶ ያሳየ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለፁ፡፡
በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተጀመረው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የመልማት አቅማቸውን ወደ ተግባር በመለወጥ ለትውልድ የሚሻገር ሰው ተኮር የልማት ውጤቶች እንዲመዘገቡ እያደረገ ነው።
የዚሁ አካል የሆነው የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማትም ተፈጥሯዊ ሀብቶቿን በማልማት ፈጣን ዕድገት እንድታስመዘግብ አድርጓል።

የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የከተማዋ የኮሪደር ልማት በተፈጥሮ ከታደለቻቸው ሐይቅና ተራሮች ጋር የተሳሰረና በፕላን ላይ የተመሰረተ ሰው ተኮር ልማት እንዲተገበር አግዟል።
ልማቱ ሰፋፊ መንገዶችና አረንጓዴ ሥፍራዎች እንዲስፋፉ በማድረግ በከተማዋ የጎብኚዎች ቁጥር እንዲጨምርና ለሥራና ለኑሮ ተመራጭ ከተማ እንድትሆን ማድረጉን ተናግረዋል፡፡
በኮሪደር ልማቱ የተገነቡ የእግረኛና ብስክሌት መንገዶች ሀዋሳ ቀድሞ የነበራትን የብስክሌት ባህል ዳግም እንዲያንሰራራ ያደረገ መሆኑን ከንቲባው ጠቁመዋል፡፡
የሕፃናት መጫወቻዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ የብስክሌት መንገዶች፣ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ የታክሲ መጫኛና ማውረጃዎች እንዲሁም ሌሎች ከተማዋን ዘመናዊነት የሚያላብሱ ሥራዎች በኮሪደር ልማቱ መካተታቸውንም ገልጸዋል፡፡
ልማቱን ከቱሪስት መዳረሻ ተፈጥሯዊ መስህቦቿ ጋር እንዲተሳሰር ለማድረግም የሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ መጀመሩን ጠቅሰዋል፡፡

የሀዋሳ ከተማ ለመዝናኛ ተመራጭ የሚያደርጋት ተፈጥሯዊና ሰውሰራሽ መስህቦች ባለቤት እንደሆነች የተናገሩት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ወጋየሁ ሰለሞን ናቸው።
አሁን ላይ እየተሰሩ ያሉ የሕፃናት መዝናኛ ሥፍራዎችም ይህን አቅሟን የሚያሳድጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

ቀደም ሲል የቆሸሹ አካባባዎችና ለወንጀል መፈጸሚያ ምቹ የነበሩ ቦታዎች ጭምር ወደ ልማት መግባታቸው የከተማዋን እድገት ለመፋጠን ካላቸው ፋይዳ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን እያሳደጉ ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማቱ ቀደም ሲል በከተማዋ የነበረውን ጠባብ የእግረኛ መንገድ ማስቀረቱ የሚበረታታ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ይሄይስ ወንድሙ የተባሉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ናቸው።

ይህም በእግር በመንቀሳቀስ ጤናን ለመጠበቅና የከተማዋን የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ ማገዙን ጠቁመዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የዜጎችን ጤና ለመጠበቅና በከተማዋ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች እንዲነቃቁ ማገዙን አስረድተዋል፡፡
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026