🔇Unmute
ሰቆጣ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦የዋግ ኽምራ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዲጂታል አሰራር ስርዓት በመዘርጋት ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠቱ ከእንግልትና ወጪ ታድጎናል ሲሉ ተገልጋዮች ገለፁ።
በፍርድ ቤቱ የዲጂታል አገልግሎት ሲገለገሉ የነበሩት አቶ ጌጡ ግርማይ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በከፍተኛ ፍርድ ቤት የነበራችውን የሕግ ጉዳይ ለደሴ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ማቅረባቸውን ይናገራሉ።
የሰቆጣ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጌጡ በብሔረሰብ አስተዳደሩ የሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዘረጋው የዲጂታል አገልግሎት በመጠቀም ጉዳያቸውን እየተከታተሉ መሆኑን ነው የሚገልጹት።
ጉዳያቸውን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ባሉበት ቦታ ሆነው መከታተል መቻላቸውም ወደ ደሴ ከተማ ለመጓዝ የሚያስፈልጋቸውን ገንዘብ፣ ጉልበትና ጊዜ ለመቆጠብ እንዳስቻላቸው ይናገራሉ።
በብሔረሰብ አስተዳደሩ የፃግብጅ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ካሱ ወርቅነህ በበኩላቸው፤ ለ4ኛ ጊዜ የጠቅላይ ፍርድ ቤት አገልግሎትን ለማግኘት ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ እንደመጡ ገልፀዋል።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን አገልግሎት ለማግኘት ደሴ ከተማ ድረስ መጓዝ ይጠበቅባቸው የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን በተዘረጋው የዲጂታል አሰራር በአቅራቢያቸው መገልገል መቻላቸውን ጠቁመዋል።
አገልግሎቱ መጀመሩ በአጠቃላይ ለትራንስፖርት፣ ለምግብ፣ ለማረፊያና ሌሎች አገልግሎቶች ያወጡት የነበረውን እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ ለማዳን እንዳስቻላቸው ነው የሚናገሩት።
የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ጌታነህ ጥጋቡ እንደገለጹት፤ ፍርድ ቤቱ የዲጂታል አሰራርን በመከተል በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ተችሏል።

በተለይም ባለጉዳዮች ለጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ይግባኝ ለማቅረብ ወደ ደሴና ባህርዳር ከተሞች ያደርጉት የነበረውን ጉዞ፣ እንግልትና ወጪ ያስቀረ መሆኑን አስረድተዋል።
አገልግሎቱ መጀመሩ ባለጉዳዮች ይግባኝ የተጠየቁባቸው 220 የወንጀልና የፍትሐብሄር መዝገቦችን በዲጂታል የዳኝነት ስርዓት ውሳኔ እንዲያገኙ በማድረግ ሊያወጡ የነበረውን 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ማዳን ተችሏል ብለዋል።
ይህም በአቅም ማነስ ምክንያት የይግባኝ ስርዓት ለማቅረብ የማይችሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ችግር በዘላቂነት የፈታ አሰራር መሆኑን ነው የተናገሩት።
ፍርድ ቤቱ የዲጂታል አሰራርን በመከተሉ ቀልጣፋና ፍትሃዊ ውሳኔ ከመስጠት ባሻገር አሰራሩን ከወረቀት ንክኪ ነጻ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026