የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ፍርድ ቤቱ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራር ስርዓት መከተሉ ከእንግልትና ወጪ ታድጎናል

Jun 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰቆጣ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦የዋግ ኽምራ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዲጂታል አሰራር ስርዓት በመዘርጋት ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠቱ ከእንግልትና ወጪ ታድጎናል ሲሉ ተገልጋዮች ገለፁ።

በፍርድ ቤቱ የዲጂታል አገልግሎት ሲገለገሉ የነበሩት አቶ ጌጡ ግርማይ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በከፍተኛ ፍርድ ቤት የነበራችውን የሕግ ጉዳይ ለደሴ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ማቅረባቸውን ይናገራሉ።

የሰቆጣ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጌጡ በብሔረሰብ አስተዳደሩ የሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዘረጋው የዲጂታል አገልግሎት በመጠቀም ጉዳያቸውን እየተከታተሉ መሆኑን ነው የሚገልጹት።

ጉዳያቸውን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ባሉበት ቦታ ሆነው መከታተል መቻላቸውም ወደ ደሴ ከተማ ለመጓዝ የሚያስፈልጋቸውን ገንዘብ፣ ጉልበትና ጊዜ ለመቆጠብ እንዳስቻላቸው ይናገራሉ።

በብሔረሰብ አስተዳደሩ የፃግብጅ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ካሱ ወርቅነህ በበኩላቸው፤ ለ4ኛ ጊዜ የጠቅላይ ፍርድ ቤት አገልግሎትን ለማግኘት ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ እንደመጡ ገልፀዋል።


የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን አገልግሎት ለማግኘት ደሴ ከተማ ድረስ መጓዝ ይጠበቅባቸው የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን በተዘረጋው የዲጂታል አሰራር በአቅራቢያቸው መገልገል መቻላቸውን ጠቁመዋል።

አገልግሎቱ መጀመሩ በአጠቃላይ ለትራንስፖርት፣ ለምግብ፣ ለማረፊያና ሌሎች አገልግሎቶች ያወጡት የነበረውን እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ ለማዳን እንዳስቻላቸው ነው የሚናገሩት።

የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ጌታነህ ጥጋቡ እንደገለጹት፤ ፍርድ ቤቱ የዲጂታል አሰራርን በመከተል በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ተችሏል።


በተለይም ባለጉዳዮች ለጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ይግባኝ ለማቅረብ ወደ ደሴና ባህርዳር ከተሞች ያደርጉት የነበረውን ጉዞ፣ እንግልትና ወጪ ያስቀረ መሆኑን አስረድተዋል።

አገልግሎቱ መጀመሩ ባለጉዳዮች ይግባኝ የተጠየቁባቸው 220 የወንጀልና የፍትሐብሄር መዝገቦችን በዲጂታል የዳኝነት ስርዓት ውሳኔ እንዲያገኙ በማድረግ ሊያወጡ የነበረውን 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ማዳን ተችሏል ብለዋል።

ይህም በአቅም ማነስ ምክንያት የይግባኝ ስርዓት ለማቅረብ የማይችሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ችግር በዘላቂነት የፈታ አሰራር መሆኑን ነው የተናገሩት።

ፍርድ ቤቱ የዲጂታል አሰራርን በመከተሉ ቀልጣፋና ፍትሃዊ ውሳኔ ከመስጠት ባሻገር አሰራሩን ከወረቀት ንክኪ ነጻ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026