የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ዘላቂና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይልን በሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ስትራቴጂ እየተዘጋጀ ነው

Jun 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦ዘላቂና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይልን በሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ስትራቴጂ እየተዘጋጀ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት መርሃ ግብር ምዕራፍ ሦስት ትግበራን የተመለከተ አውደጥናት አካሂዷል።


በዚህ ወቅት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ለዕድገትና ለማንኛውም ዓይነት የልማት እንቅስቃሴ ወሳኝ ነው።

በተመጣጣኝ ዋጋ የሚቀርብ ታዳሽ፣ ዘላቂና አስተማማኝ የኃይል ተደራሽነት የኢትዮጵያን ብልፅግና፣ ዕድገትና ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ ያሏትን የኃይል አማራጭ ምንጮች ለመጠቀም የኃይል ማመንጨት አቅምን ማሳደግ፣ እንዲሁም የኃይል አማራጮችን የማሻሻል ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ገልጸዋል።

ለብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት መርሃ ግብር ትግበራ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ እንዲያድግ ለማድረግ የኢነርጂ ፖሊሲ ክለሳ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በተጨማሪም መንግሥት ዘርፉን ለማጠናከር በርካታ ስትራቴጂዎችንና የሕግ ማዕቀፎችን ማዘጋጀቱን ጠቅሰዋል።

የመጀመሪያውና ሁለተኛው የኤሌክትሪክ ተደራሽነት መርሃ ግብር ትግበራ ከዋናው መስመር ርቀው ባሉ አካባቢዎች የሶላር ቴክኖሎጂዎችን ለገጠሩ ማኅበረሰብ ተደራሽ በማድረግ ረገድ መሻሻል ያመጣ መሆኑን አብራርተዋል።

በመርሃ ግብሩ የሦስተኛው ምዕራፍ ትግበራም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ንጹሕ ኢነርጂን ማስፋፋት፣ ለምርታማነት ተግባራት ቅድሚያ መስጠትና የዘርፉን ዲጂታላይዜሽን አሠራር ማጠናከር ላይ የሚያተኩር መሆኑን ተናግረዋል።

ለዚህ ምዕራፍ ትግበራ ከ18 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልግ ጠቁመው በሁለቱ ምዕራፎች ያጋጠሙ ክፍተቶችን ለመፍታት በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።

ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን በማጠናከር ለሌሎች የአፍሪካ አገራት ኃይል በማቅረብ የአህጉሪቱን ሁለንተናዊና የተቀናጀ ልማት በማሳለጥ ቀጣናዊና አህጉራዊ የኢኮኖሚ ውህደትን ለማጠናከር እየተሠራ መሆኑንም አስረድተዋል።


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፤ የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ሥራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ ትግበራ እስከ 2035 ድረስ ባሉት ዓመታት የኤሌክትሪክ ኃይልን በመላ አገሪቱ ለማዳረስ መታቀዱን የገለጹት ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ናቸው።


በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኤሌክትሪፊኬሽንና ኢነርጂ መረጃ መሪ ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ዳቢ፤ የብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን የሚመራ ስትራቴጂ ለማዘጋጀት ከአንድ ዓመት በላይ ጥናት ሲካሄድ ቆይቷል ብለዋል።


በስትራቴጂው የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት መንግሥት፣ ከልማት አጋሮችና ከግሉ ዘርፍ ጋር በትብብር እንደሚሠራም ገልጸዋል።

የዓለም ባንክ የኢነርጂ ባለሙያ ወንድአየሁ ደምሴ በበኩላቸው፤ ባንኩ በኢነርጂ ዘርፍ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በትብብር እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።


አሁንም በብሔራዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት መርሃ ግብር የቴክኒክ ድጋፍ ማድረጉንና በቀጣይም ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026